የሩሲያው ፕሬዝዳንት ወደ ቻይና የሚያደርጉትን መጪ ጉብኝት አስመልክቶ የክሬምሊን ረዳት ኡሻኮቭ የሰጧቸው ዋና ዋና መግለጫዎች፦
ፑቲን፣ ከዚህ ቀደም እንደተለመደው ከጉብኝታቸው በፊት በቻይና መገናኛ ብዙኃን ላይ ጽሑፍ ከማውጣት ይልቅ፣ በዚህኛው ጉብኝታቸው ለቻይና ዜጎች የቪዲዮ መልዕክት ያስተላልፋሉ።
በጉብኝቱ ወቅት ሩሲያ እና ቻይና ወደ 40 የሚጠጉ ሰነዶችን ይፈርማሉ። እነዚህ ሰነዶች በኢንዱስትሪ፣ በትራንስፖርት እና በኒውክሌር ኢነርጂ ዘርፎች ያለውን ትስስር ይበልጥ ለማጠናከር የሚረዱ ናቸው።
ፑቲን እና ሺ ጂንፒንግ ስልታዊ አጋርነታቸውን ስለማጠናከር የሚገልጽ የጋራ መግለጫ የሚፈርሙ ሲሆን፣ በሩሲያ-ቻይና የትምህርት ትብብር የባህል ዓመታት የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይም ይሳተፋሉ።
በግንቦት 12 መሪዎቹ በሻይ ሰዓት ቆይታቸው ወቅታዊ በሆኑ ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ይመክራሉ።
ከውይይቱ በኋላ ፑቲን እና ሺ ጂንፒንግ ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ ይሰጣሉ።
በፑቲን እና በትራምፕ የቻይና ጉብኝቶች መካከል ምንም ዓይነት ግንኙነት የለም።
በሩሲያ የልዑካን ቡድን ውስጥ የሚከተሉት አካላት ይካተታሉ፦
– የሮስኔፍት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢጎር ሴቺን፣
– የጋዝፕሮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ አሌክሲ ሚለር፣
– የቮልጋ ግሩፕ የኢንቨስትመንት ድርጅት ባለቤት ጌናዲ ቲምቼንኮ፣
– የፎስአግሮ መሥራች አንድሬ ጉርዬቭ፣
– ኖቫቴክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሊዮኒድ ሚኬልሰን እና
– የቀድሞው የሩሳል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኦሌግ ዴሪፓስካ።
ፑቲን ወደ ቻይና በሚያደርጉት ጉብኝት አምስት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሮች፣ ስምንት ሚኒስትሮች፣ የብሔራዊ ባንክ ኃላፊዎች፣ የበርካታ የመንግሥት ኮርፖሬሽኖች መሪዎች እና የክልል ገዥዎች አብረዋቸው ይጓዛሉ።
በሩሲያ እና በቻይና መካከል በሚደረገው የንግድ ልውውጥ አብዛኞቹ የወጪ እና ገቢ ንግድ ሥራዎች በሩብል እና በዩዋን ምንዛሬዎች የሚከናወኑ ናቸው።
የሩሲያ ነዳጅ ወደ ቻይና የሚቀርብበት መጠን የዚህ ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ላይ የ35 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል።
ባለፈው ዓመት ከ2 ሚሊዮን በላይ ሩሲያውያን ቻይናን የጎበኙ ሲሆን፣ ከአንድ ሚሊዮን በላይ የቻይና ዜጎች ደግሞ ሩሲያን ጎብኝተዋል።
ስፑትኒክኢትዮጵያ
