ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ መሶብ የአንድ ማዕከል የሙከራ አገልግሎትን ትላንት ቅዳሜ እለት አስጀምረዋል።
አገልግሎቱ “ዜጎች ጊዜያቸውን እንዲቆጥቡ እና አገልግሎቶችን በተሻለ ውጤታማ መንገድ ለማግኘት ያግዛቸዋል” ሲሉ በማህበራዊ ትሥሥር ገፃቸው ተናግረዋል።
መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በአንድ ጣራ ስር የተለያዩ የመንግስት አገልግሎቶችን በማጣመር የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የሚሰጥበት መሆኑ ተገልጿል
በአጠቃላይ በፓይለት ፕሮግራም በአንድ ስፍራ የ12 ተቋማት 41 አገልግሎቶች በመሰጠት ላይ ይገኛሉ።
እነዚህም ፡
- የብሄራዊ መታወቂያ አገልግሎት
- የኢሚግሬሽን እና የዜግነት አገልግሎት
- የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሌት
- የገቢዎች ሚኒስቴር
- የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር
- የስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር
- የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን
- የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር
- የትምሀርት ምዘና እና ፍተናዎች አገልግሎት
- የኢትዮ ፖስታ
- የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
- ኢትዮ ቴሌኮም
ሀሉም ተቋማት በቴክኖሎጂ አማካኝነት በትስስር አገልግሎት እየሰጡም ይገኛሉ።መሶብ ትናንት በጠቅላይ ሚንስተር አብይ ተመርቆ ወደ ስራ ገብቷል።
