12 የኢትዮጵያና ኤርትራ ከፍተኛ ባለሥልጣናትና ወታደራዊ አዛዦች በጀርመን በጦር ወንጀል ተከሰሱ

Date:

አንድ የቀድሞ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ሃላፊንና አንድ የቀድሞ የረድኤት ሠራተኛ በ12 የኢትዮጵያና ኤርትራ ከፍተኛ ባለሥልጣናትና ወታደራዊ አዛዦች በትግራይ “የጦር ወንጀል” እና “በሰብዓዊነት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች” ፈጽመዋል በማለት ለጀርመን ዓቃቤ ሕግ ክስ አቀረቡ።

ከቀድሞ የአስተዳደሩ ሃላፊ እና የረድኤት ሠራተኛው በተጨማሪ ስምንት የትግራይ ተወላጆች ክሱን በጋራ አቅርበዉታል።

የወንጀሎቹ ሰለባና ወንጀሎቹ ሲፈጸም እማኝ የነበሩት አቤቱታ አቅራቢዎቹ፣ የጀርመን ፌደራል ዓቃቤ ሕግ በወንጀሎቹ ላይ የምርመራ መዝገብ እንዲከፍትና በአገሪቱ ፍርድ ቤት ክስ እንዲመሠርት ጠይቀዋል።

ግለሰቦቹ አቤቱታውን ያቀረቡት፣ ሌጋል አክሽን ወርልድዋይድ በተሰኘ የሕግ ተቋምና ሌሎች ድርጅቶችና የሕግ ባለሙያዎች ድጋፍ ነው።

የጀርመን ዓቃቤ ሕግ በውጭ አገራት በተፈጸሙ ዓለማቀፍ አስከፊ ወንጀሎች ዙሪያ ምርመራ የማድረግ ሥልጣን አለው።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...