14 ሲቪል ማኅበራት 12 መገናኛ ብዙኃንን በመጠቀም የመራጮች ትምህርት እየሰጡ እንደሆነ ተገለጸ

Date:

ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ለሚካሔደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ ለመስጠት ካርድ የወሰዱ መራጮች በቂ የመራጭነት ግንዛቤ እንዲኖራቸው 12 መገናኛ ብዙኃንን በመጠቀም እና በዋና ዋና አደባባዮች በመንቀሳቀስ የመራጮች ትምህርት እየተሰጠ እንደሆነ የኢትዮጵያ ሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች ሕብረት ለምርጫ አስታውቋል።

የሕብረቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ አበራ ኃይለማርያም እንደገለጹት፦

መራጮች በምርጫው ወቅት ማድረግ ያለባቸውን እና የሌለባቸውን ድርጊቶች በመግለጽ ትምህርት በመስጠት ላይ እንደሆኑ ተናግረዋል።

የመራጮች ትምህርት እየተሰጠባቸው ከሚገኙ 12 የብዙኃን መገናኛ አውታሮች መካከል አስሩ የክልል መገናኛ ብዙኃን ሲሆኑ ቀሪዎቹ ሀገር አቀፍ ተደራሽነት ያላቸው ናቸው ተብሏል።

በተለያዩ የኢትዮጵያ ክልሎች የሚገኙት 10 መገናኛ ብዙኃን የመራጮች ትምህርት በመስጠት ላይ የሚገኙት ሚድያዎች እንደሚገኙበት ክልል በተለያዩ ቋንቋዎች መራጮችን የማንቃት ስራ እየሰሩ ሲሆን፤ ቀሪዎቹ ሁለቱ ደግሞ ሀገር አቀፍ ተደራሽነት ያላቸው ናቸው ተብሏል።

ከመደበኛ መገናኛ ብዙኃን በተጨማሪ በማኅበራዊ ትስስር ገጾች በምርጫ ወቅት የተከለከሉ ሕጎችን የማሳወቅ ስራ ተሰርቷል ተብሏል።

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰላም እና በስኬት እንዲጠናቀቅ 14 የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች በቅንጅት እየሰሩ እንደሆነ የሕብረቱ ዋና ዳይሬክተር አብራርተዋል።

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...