“የአፍሪካን የጤና ባለሙያዎች ኃይል ለመጪው ግዜያት ማዘጋጀት፦ አጋርነትን፣ ቴክኖሎጂን፣ ፈጠራን እና አመራርን መጠቀም” በሚል መሪ ቃል የሚካሄደው ጉባኤው በአኅጉሪቱ የሕክምና ትምህርትን ለማሳደግ እና የጤና ባለሙያዎችን አቅም ለማጠናከር ያለመ ነው።
የኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር ከአፍሪካ የሕክምና ትምህርት ቤቶች ጥምረት እና ከግሎባል ሄልዝ ኢክዊቲ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ያዘጋጁት ይህ ጉባኤ ለወደፊት ፈተናዎች ዝግጁ የሆነ የጤና ባለሙያ ኃይል ለመገንባት፣ በአፍሪካውያን የሚመሩ የፈጠራ መፍትሔዎችን ማሳደግ ላይ ያተኩራል ተብሏል።
የአፍሪካ የሕክምና ትምህርት ጉባኤ (ሜድኤድአፍሪካ 2026) በአፍሪካ የሕክምና ትምህርት ጥራትን ለማሻሻል እና የጤና ሥርዓቶችን ለማጠናከር በተግባራዊነት፣ በፈጠራ እና በስትራቴጂካዊ አጋርነቶች ላይ በትኩረት እንደሚሰራ መገለፁን የስፑትኒክ ባልደረባ ዘግቧል።
👉 ለሁለት ቀናት በሚቆየው በዚህ ጉባኤ ላይ ከ46 ሀገራት እና ከ117 ተቋማት የተውጣጡ ከ750 በላይ ባለድርሻአካላት እየተካፈሉ ሲሆን፤ ይህም በአኅጉሪቱ በሕክምና ትምህርት ዘርፍ ከተደረጉ ትላልቅ ስብሰባዎች አንዱ ያደርገዋል።
