Date:

የአል-ነጃሺ መስጅድ ቅርስ ጥገና በመጋቢት ወር ይጠናቀቃል ተባለ።

መስከረም ወር ላይ  የቅርሱ የእድሳት ስራዉ የተጀመረ ሲሆን  ከ 90 በመቶ ስራዉ መጠናቀቅ መቻሉን ሰምተናል።

ከመስከረም ወር አንስቶ የቅርሱ ጥገና ለማስጀመር ጥረቶች ሲደረጉ መቆየታቸውን የገለፁት የትግራይ ቱሪዝም ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ሀይላል በየነ በመጪዉ መጋቢት ወር ጥገናዉን እንደሚጠናቀቅለት ገልፀዋል።

በሰሜኑ ጦርነት የቅርሱ ይዞታ  የከባድ መሳሪያ ጥቃት ሰለባ በመሆኑ የቅርሱን ጥገና በጥንቃቄ ለመስራት ተሞክሯል ተብሏል።

የቅርሱ የእድሳት ስራ ምእራፉን ለማጠናቀቅ ጥቂት ቀሪ ስራዎች ብቻ ቀርተዉታል ነዉ የተባለዉ።

አቶ ሀይላይ ቅርሱን ሀይማኖታዊ አዉዱን  እንዳያጣ ለማድረግ የክልሉ የእስልምና ጉዳዩች በቅርበት ሲከታተለዉ ቆይቷል ብለዋል።

የቅርስ እድሳት ስራዉ በወጪ ደረጃ  የቱርክ ልማት ኤጀንሲ የሸፈነ ሲሆን ቅርስ ጥገናዉን የቴክኒክ እና የማማከር ስራዎችን የቱሪዝም ቢሮዉ እንደከወነ ተናግረዋል።

በትግራይ ክልል የሚገኘዉ የአልነጃሺ ታሪካዊና ሀይማኖታዊ መካነ ቅርስ ሶስት አመታት በዘለቀዉ ጦርነት ቅዱስ እቃዎች እንዲሁም በመስጅዱ የተቀመጡ የቅርስ ይዘት ያላቸዉ መገልገያዎች መዘረፋቸዉን ይታወቃል።

@ኢትዮ ኤፍ ኤም

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት በዛሬ ዕትሟ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ነሔሴ 16 2018 ዓ.ም ገበያ...

ቱርክ ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ የእስር ማዘዣ አወጣች

ቱርክ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ ዓለም አቀፍ...

በመቀለ የሚካሄደው የአሸንዳ በዓል የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ተሰረዘ

በትግራይ በርካታ ታዳሚ በሚገኝበት በየዓመቱ የሚከበረው የአሸንዳ ባህላዊ በዓል...

የኢትዮጵያ ፖስታ 3 ሺሕ የሚጠጉ ቅርንጫፎቹን ወደ ባንክ ኤጀንትነት ለመቀየር እንቅስቃሴ ጀመረ

የኢትዮጵያ ፖስታ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ 3 ሺሕ በሚጠጉ ቅርንጫፎቹ...