Date:

የአል-ነጃሺ መስጅድ ቅርስ ጥገና በመጋቢት ወር ይጠናቀቃል ተባለ።

መስከረም ወር ላይ  የቅርሱ የእድሳት ስራዉ የተጀመረ ሲሆን  ከ 90 በመቶ ስራዉ መጠናቀቅ መቻሉን ሰምተናል።

ከመስከረም ወር አንስቶ የቅርሱ ጥገና ለማስጀመር ጥረቶች ሲደረጉ መቆየታቸውን የገለፁት የትግራይ ቱሪዝም ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ሀይላል በየነ በመጪዉ መጋቢት ወር ጥገናዉን እንደሚጠናቀቅለት ገልፀዋል።

በሰሜኑ ጦርነት የቅርሱ ይዞታ  የከባድ መሳሪያ ጥቃት ሰለባ በመሆኑ የቅርሱን ጥገና በጥንቃቄ ለመስራት ተሞክሯል ተብሏል።

የቅርሱ የእድሳት ስራ ምእራፉን ለማጠናቀቅ ጥቂት ቀሪ ስራዎች ብቻ ቀርተዉታል ነዉ የተባለዉ።

አቶ ሀይላይ ቅርሱን ሀይማኖታዊ አዉዱን  እንዳያጣ ለማድረግ የክልሉ የእስልምና ጉዳዩች በቅርበት ሲከታተለዉ ቆይቷል ብለዋል።

የቅርስ እድሳት ስራዉ በወጪ ደረጃ  የቱርክ ልማት ኤጀንሲ የሸፈነ ሲሆን ቅርስ ጥገናዉን የቴክኒክ እና የማማከር ስራዎችን የቱሪዝም ቢሮዉ እንደከወነ ተናግረዋል።

በትግራይ ክልል የሚገኘዉ የአልነጃሺ ታሪካዊና ሀይማኖታዊ መካነ ቅርስ ሶስት አመታት በዘለቀዉ ጦርነት ቅዱስ እቃዎች እንዲሁም በመስጅዱ የተቀመጡ የቅርስ ይዘት ያላቸዉ መገልገያዎች መዘረፋቸዉን ይታወቃል።

@ኢትዮ ኤፍ ኤም

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አቶ ይህንዓለም አቅናው የአማራ ባንክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሆኑ

በኢትዮጵያ በፍጥነት እያደጉ ከሚገኙ እና ከፍተኛ የባለአክስዮኖች ቁጥር ካላቸው...

ማዕቀቦች የኢራንን የኒውክሌር መርሃ-ግብር ቢያደናቅፉም መንግስቱን ሊጥሉ እንደማይችሉ ተገለጸ

ማዕቀቦች የኢራንን ወታደራዊ እና የኒውክሌር እንቅስቃሴዎች አስቸጋሪና ውድ እንዲሆኑ...

የአፍሪካ ሀገራት አዲስ የኢንቨስትመንት ፈንድ ይፋ አደረጉ

በአፍሪካ ሀገራት ላይ የተደቀነውን ከፍተኛ የብድር ጫና ለማቃለል እና...

ዶናልድ ትራምፕ “በቅርቡ” ሆርሙዝ የአሜሪካ ግዛት አካል እንደሚሆን ተናገሩ

ከኢራን ጋር ያለው ግጭት እየተባባሰ ባለበት በአሁኑ ሰዓት የአሜሪካው...