Date:

ምክር ቤቱ የአንድ የምክር ቤት አባልን ያለመከሰስ መብት አነሳ

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት የአንድን የምክር ቤት አባል ያለመከሰስ መብት አንስቷል፡፡

ምክር ቤቱ ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ጉባኤው አቶ ዮሐንስ ተሰማ የተባሉ የምክር ቤት አባልን ያለመከሰስ መብት ማንሳቱ ተገልጿል።

የምክር ቤት አባሉ ግጭትን የሚቀሰቅሱ፣ የክልሉንና የምክር ቤቱን ክብር የሚነኩ መረጃዎችን በማኅበራዊ ሚዲያ ማሰራጨታቸው ተገልጿል።

በተለይም የክልሉ ምክር ቤት 6 ዙር 5ኛ ዓመት 1ኛ የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ጉባኤው ውሳኔዎችን ካሳለፈ በኋላ በዚህ ድርጊት መሳተፋቸውን የክልሉ ፍትሕ ቢሮ ኃላፊ መሐመድ ሃሚድ ለምክር ቤቱ በሰጡት ማብራሪያ ላይ ጠቅሰዋል፡፡

እኚሁ የምክር ቤት ሕዝብን ከሕዝብ የሚያነሳሳ ሀሰተኛ መረጃዎችን ማሠራጨታቸውና፣ መንግሥትን በኃይል ለመጣል ከሚጥሩ አካላት ጋር ግንኙነት እንዳላቸው አመላካች መረጃዎች መኖራቸውም ተገልጿል።

የምክር ቤቱ አባል በተጠረጠሩበት ጉዳይ በህግ ተጠያቂ እንዲሆኑ የቀረበውን ማብራሪያ ተከትሎ የክልሉ ምክር ቤት የአቶ ዮሐንስ ተሰማ ያለመከሰስ መብት እንዲነሳ በሙሉ ድምጽ ማጽደቁን የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ አመላክቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከባለፈው  ዓመት የ130 በመቶ ብልጫ  አተረፈ

መጋቢት 30 በተጠናቀቀው የኩባንያው በጀት ዓመት 15.9 ቢሊዮን ብር...

በዕውቀቱ በታላቁ ዓለም አቀፍ ፌስቲቫል ላይ ተመረጠ

ዝነኛው ደራሲና ገጣሚ በዕውቀቱ ሥዩም በስፔን ባርሴሎና በሚካሄደው 41ኛው...

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...