233 ቢሊየን ብር መሰብሰብ ተችሏል – ከንቲባ አዳነች አቤቤ

Date:

በ2017 የበጀት ዓመት 241.4 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ የነበረ ሲሆን፣ 233 ቢሊየን ብር በመሰብሰብ የዕቅዱን 96.5 በመቶ ማሳካት መቻሉን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት መልዕክት፣ ይህም ከባለፈው በጀት ዓመት 83.3 ቢሊየን ብር ብልጫ ወይም 45 በመቶ እድገት በከተማዋ ገቢ ላይ ያሳየ ነው ብለዋል።

ያልተሰበሰበው 8 ቢሊየን ብር ከእርዳታ እና ብድር ይገኛል ተብሎ በተጨማሪ በጀት የታወጀ እንደነበርም አንስተዋል።

“ለውጥና እድገት በራስ አቅም ሲሆን መሰረቱ ሰፊ፤ ምሰሶውም ጠንካራ ይሆናል” ያሉት ከንቲባዋ፣ ለተገኘዉ ስኬት የከተማዋን ነዋሪዎች፣ ግብር ከፋዮችን፣ የገቢዎች ቢሮ ሰራተኞችና አመራሮችን እንዲሁም ባለድርሻ አካላትን አመስግነዋል።

“ነገም አቅማችን እናንተዉ ናችሁና ፤ ችግሮችን እያረምን በራስ አቅም፣ በትብብር፣ በጠንካራ እምነት እና የስራ ባህል የመራናት ከተማችን እድገት ይቀጥላልም ነው ያሉት።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...

የእግር ኳስ ዳኝነት በኢትዮጵያ

ገነነ መኩሪያ (ሊብሮ) ግዮን መጽሔት :- እግር ኳስ...

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...