በ2017 የበጀት ዓመት 241.4 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ የነበረ ሲሆን፣ 233 ቢሊየን ብር በመሰብሰብ የዕቅዱን 96.5 በመቶ ማሳካት መቻሉን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት መልዕክት፣ ይህም ከባለፈው በጀት ዓመት 83.3 ቢሊየን ብር ብልጫ ወይም 45 በመቶ እድገት በከተማዋ ገቢ ላይ ያሳየ ነው ብለዋል።
ያልተሰበሰበው 8 ቢሊየን ብር ከእርዳታ እና ብድር ይገኛል ተብሎ በተጨማሪ በጀት የታወጀ እንደነበርም አንስተዋል።
“ለውጥና እድገት በራስ አቅም ሲሆን መሰረቱ ሰፊ፤ ምሰሶውም ጠንካራ ይሆናል” ያሉት ከንቲባዋ፣ ለተገኘዉ ስኬት የከተማዋን ነዋሪዎች፣ ግብር ከፋዮችን፣ የገቢዎች ቢሮ ሰራተኞችና አመራሮችን እንዲሁም ባለድርሻ አካላትን አመስግነዋል።
“ነገም አቅማችን እናንተዉ ናችሁና ፤ ችግሮችን እያረምን በራስ አቅም፣ በትብብር፣ በጠንካራ እምነት እና የስራ ባህል የመራናት ከተማችን እድገት ይቀጥላልም ነው ያሉት።
