24 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ግዢ ተፈፅሞ ወደ ሃገር ውስጥ የማጎጎዝ ስራ አየተሰራ መሆኑን ግብርና ሚኒስተር አስታውቋል
እስካሁን ባለው አፈፃፃም 8 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ወደ ሃገር ውስጥ ተጎጉዞ መአከላዊ መጋዘን መድረሱን የግብርና ሚኒስተር የህዝብ ግንኙነት ስራ አስፈፃሚ የሆኑት አቶ ከበደ ላቀው ላቀው ለጣቢያችን ተናግረዋል ::
መንግሥት ድጎማ ከሚያደርግባቸው ግብአቶች አንዱ የአፈር ማዳበሪያ መሆኑን የገለፁት የህዝብ ግንኙነት ስራ አስፈፃሚዉ 84 ቢሊዮን ብር ለአፈር ማዳበሪያ ድጎማ መደረጉን አስታዉቀዋል ፡፡
የአፈር ማዳበሪያን ከዉጭ የማጎጎዝ ሂደቱ በታቀደዉ ልክ እየሄደ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ከበደ ወደ ሃገር ዉስጥ የማስገባቱ ሂደት እስከ ሀምሌ ወር ድረስ እንደሚቀጥል ገልፀዋል ፡፡
የግብርና ሚኒስቴር ለእያንዳንዱ ክልል የሚደርሰዉን የአፈር ማዳበሪያ በመተንተን ተደራሺ እንዲሆን እየሰራ እንደሆነም ተጠቁሞል ፡፡
