24 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ግዥ መፈፀሙን ግብርና ሚኒስተር አስታወቀ

Date:

24 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ግዢ ተፈፅሞ ወደ ሃገር ውስጥ የማጎጎዝ ስራ አየተሰራ መሆኑን ግብርና ሚኒስተር አስታውቋል

እስካሁን ባለው አፈፃፃም 8 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ወደ ሃገር ውስጥ ተጎጉዞ መአከላዊ መጋዘን መድረሱን የግብርና ሚኒስተር የህዝብ ግንኙነት ስራ አስፈፃሚ የሆኑት አቶ ከበደ ላቀው ላቀው ለጣቢያችን ተናግረዋል ::

መንግሥት ድጎማ ከሚያደርግባቸው ግብአቶች አንዱ የአፈር ማዳበሪያ መሆኑን የገለፁት የህዝብ ግንኙነት ስራ አስፈፃሚዉ 84 ቢሊዮን ብር ለአፈር ማዳበሪያ ድጎማ መደረጉን አስታዉቀዋል ፡፡

የአፈር ማዳበሪያን ከዉጭ የማጎጎዝ ሂደቱ በታቀደዉ ልክ እየሄደ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ከበደ ወደ ሃገር ዉስጥ የማስገባቱ ሂደት እስከ ሀምሌ ወር ድረስ እንደሚቀጥል ገልፀዋል ፡፡

የግብርና ሚኒስቴር ለእያንዳንዱ ክልል የሚደርሰዉን የአፈር ማዳበሪያ በመተንተን ተደራሺ እንዲሆን እየሰራ እንደሆነም ተጠቁሞል ፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አዲስ ጦርነት ከተቀሰቀሰ ኢራን የበለጠ ምላሽ በመስጠት የተራዘመ ጦርነት እንደምታካሂድ አስታወቀች

ከፍተኛ የኢራን ወታደራዊ ባለሥልጣናት አሜሪካ ሌላ ዙር ጥቃት በአገራቸው...

ምክክሩ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል

ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በሥራ ቡድን ደረጃ እየተካሄደ የሚገኘውን...

የጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ 28 የውጭ ዜጋ ተማሪዎችን ከኢትዮጵያውያን ቤተሰቦች ጋር ማስተሳሰሩን ገለጸ

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ መርሃ-ግብር አማካኝነት በዘንድሮው ዓመት...

የሕግ ተማሪዎቹ አፍሪካን ወክለው ለዓለም አቀፍ የምስለ-ችሎት ፍጻሜ አለፉ

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ተማሪዎች በአህጉራዊው የዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት...