24 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ግዥ መፈፀሙን ግብርና ሚኒስተር አስታወቀ

Date:

24 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ግዢ ተፈፅሞ ወደ ሃገር ውስጥ የማጎጎዝ ስራ አየተሰራ መሆኑን ግብርና ሚኒስተር አስታውቋል

እስካሁን ባለው አፈፃፃም 8 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ወደ ሃገር ውስጥ ተጎጉዞ መአከላዊ መጋዘን መድረሱን የግብርና ሚኒስተር የህዝብ ግንኙነት ስራ አስፈፃሚ የሆኑት አቶ ከበደ ላቀው ላቀው ለጣቢያችን ተናግረዋል ::

መንግሥት ድጎማ ከሚያደርግባቸው ግብአቶች አንዱ የአፈር ማዳበሪያ መሆኑን የገለፁት የህዝብ ግንኙነት ስራ አስፈፃሚዉ 84 ቢሊዮን ብር ለአፈር ማዳበሪያ ድጎማ መደረጉን አስታዉቀዋል ፡፡

የአፈር ማዳበሪያን ከዉጭ የማጎጎዝ ሂደቱ በታቀደዉ ልክ እየሄደ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ከበደ ወደ ሃገር ዉስጥ የማስገባቱ ሂደት እስከ ሀምሌ ወር ድረስ እንደሚቀጥል ገልፀዋል ፡፡

የግብርና ሚኒስቴር ለእያንዳንዱ ክልል የሚደርሰዉን የአፈር ማዳበሪያ በመተንተን ተደራሺ እንዲሆን እየሰራ እንደሆነም ተጠቁሞል ፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...