44 ሚሊየን በላይ ኢትዮጵያውያን የንጹህ የመጠጥ ውኃ አቅርቦት እንደሌላቸው ተገለጸ

Date:

“World Population Review” በ2025 ኢትዮጵያ ዝቅተኛ የመጠጥ ውሃ ጥራት ካላቸው ሃገራት መካከል አንዷ ነች ብሏል። በዚህም ለኢትዮጵያ 19.2/100 ውጤት ተሰጥቷታል።

ንፁህ ያልሆነን ውሃ ከሚጠጡ 100,000 ሰዎች ውስጥ ምን ያህሉ ዕድሜውን ከውሃው ጋር በተያያዘ እንደሚያጣ መሰረት በማድረግ መለኪያው የተሰራ ሲሆን እንደ ጀርመን፣ ዩናይትድ ኪንግደም፣ ጣልያንና ግሪክ ያሉ ሃገራት 100 ተሰጥቷቸው፥ ዜጎቻቸው ንፁህ ውሃ የሚጠጡባቸው ሀገራት ተብለዋል።

በዝርዝሩ ዝቅተኛው ነጥብ የተሰጣቸው 10 ሃገራት ሙሉ ለሙሉ ከአኅጉራችን አፍሪካ ናቸው።

ኢትዮጵያ አሁንም 44 ሚሊየን በላይ ዜጎቿ የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት እንደሌላቸው በዝርዝሩ ሲመላከት ይህም 42.7% ህዝቧን መሆኑ ተገልጿል።

በተጨማሪ የንፁህ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ባለመኖሩ ሰዎች ከመጠጥ ውሃ ጋር በተያያዘ ለሚፈጠሩ በሽታዎች የሚጋለጡባትም ነች ተብሏል።

44 ሚሊየን ዜጎቿ የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት አያገኙባትም የተባለችው ኢትዮጵያ ከናይጄሪያ 60.1 ሚሊየን ህዝብ በመቀጠልም ብዙ ሰዎች ንፁህ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት የማያገኙባት አፍሪካዊ ሀገር ነች።

@TikvahethMagazine

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...