የሂሳብ ትምህርት ውድድሩ ከሁሉም ክልሎች እና የከተማ አስተዳደሮች የተውጣጡ ተማሪዎቾ የሚሳተፉበት ሲሆን ውድድሩን ያሸነፉ 50 ሺህ ብር ይሸለማሉ ተብሏል።
ሁለተኛና ሶስተኛ ለወጡ ደግሞ 45 ሺህ እና 40 ሺህ ብር ያገኛሉ ነው የተባለው።
በዚህ ውድድር ከ3ኛ ክፍል እስከ 12ኛ ክፍል ያሉ 6 ሺህ ተማሪዎች እንደሚሳተፉበት ተነግሯል።
ከ3ኛ እስከ 8ኛ ክፍል ያሉት በሀገሪቱ ባሉ 23 የአፍ መፍቻ ቋንቋዎቾ ፈተናውን የሚወስዱ ሲሆን ከ9 እስከ 12ኛ ክፍል ያሉት ደግሞ በእንግሊዘኛ ይፈተናሉ ተብሏል።
ከገንዘብ ሽልማት ባለፈ የሰርተፊኬት እና የዋንጫ ሽልማት ይኖረዋል ተብሏል።
በውድድሩ በአጠቃላይ ከ2 ነጥብ 8 ሚሊየን ብር በላይ የጥሬ ገንዘብ ለሽልማት የወጣ ሲሆን ይህም እንደሀገር ከናይጄሪያ እና ደቡብ አፍሪካ ቀጥሎ ከፍተኛ መሆኑ ተጠቁሟል።
ከ80 ከተሞች የተውጣጡ ተማሪዎች በየከተማው ከየካቲት ወር ጀምሮ የዙር ውድድር አድርገው ከፍተኛ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች ሐምሌ 30 ቀን አዲስ አበባ የሚገቡ ሲሆን በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና በ4 ኪሎ ካምፓስ ያርፋሉ ተብሏል።
ውድድሩ ከነሐሴ 1 እስከ ነሐሴ 3 ቀን 2017 ዓ.ም የሚደረግ ሲሆን መዝጊያቅ በሚሊኒየም አዳራሽ ይከናወናል ተብሏል።
(አራዳ ኤፍ ኤም)
