63 ሚሊዮን ኢትዮጲያውያን የጤና መድህን አገልግሎት ተጠቃሚ ሆነዋል

Date:

በሀገር አቀፍ ደረጃ የጤና መድህን አገልግሎትን በፍትሃዊነት ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ጤና መድህን አገልግሎት አስታውቋል፡፡

አገልግሎቱ ከሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ እና ከአምርፍ ጤና አፍሪካ ጋር በመተባበር በ2018 የእቅድ አተገባበር ላይ ያተኮረ መድረክ በሀዋሳ ከተማ አካሂዷል።

የኢትዮጵያ ጤና መድህን አገልግሎት ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ ላምሮት አንዱአለም በመድረኩ ላይ እንዳሉት፥ በሀገር ደረጃ 63 ሚሊየን ዜጎች የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት ተጠቃሚ ሆነዋል፡፡

በሀገር አቀፍ ደረጃ አገልግሎቱን በፍትሃዊነት ተደራሽ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው፥ በቀጣይ የተጠቃሚዎችን ቁጥር ለማሳደግ ክልሎች በትኩረት ሊሰሩ ይገባል ብለዋል።

ባለፈው ዓመት አገልግሎቱን ለማቅረብ ከተገልጋዮች ከተሰበሰበው 19 ቢሊየን ብር በተጨማሪ 7 ቢሊዮን ብር በመንግስት መሸፈን ተችሏል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...