7ኛው ምርጫ ትግራይን ጨምሮ በመላ የሀገሪቱ ይካሄዳል

Date:

ቀጣዩን ሰባተኛው ዙር ሀገር አቀፍ ምርጫ ትግራይ ክልልን ጨምሮ በሁሉም የሀገሪቱ አከባቢዎች ለማካሄድ ዝግጅቶች እየተከናወኑ መሆናቸውን ምርጫ ቦርድ አስታወቀ።

የቦርዱ ሰብሳቢ የሆኑት ሜላተወርቅ ኃይሉ ባሳለፍነው ሳምንት ሀሙስ ሐምሌ 10 ቀን 2017 ዓ.ም ተሻሽሎ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በጸደቀው “የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ” ዙርያ ለመገናኛ ብዙኃን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።

ከነባሩ አዋጅ ውስጥ 26ቱ ድንጋጌዎች ላይ ማሻሻያ መደረጉን ያስታወቁት ሰብሳቢዋ፤ አያይዘውም በሰባተኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ተግባራዊ ለማድረግ እና የወጣቶች እንዲሁም የሴቶች ተሳትፎን በሚያረጋግጥ መልኩ መሻሻሉን ጠቁመዋል።

ችግሮች ሲፈጠሩም የፓርቲዎች፣ የምርጫ ቦርድ እና የገዢው ፓርቲ አባላት የሚገኙበት የሶስትዮሽ ኮሚቴ ተቋቁሞ በውይይት እንዲፈታ በመደረግ ላይ መሆኑንም አክለዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኮሪያ ዘማቾች ያስመዘገቡት አኩሪ ታሪክ በዓለም ሲታወስ ይኖራል

75ኛ ዓመት የኮሪያ ዘማቾች መታሰቢያ በዓል አዲስ አበባ በሚገኘው...

አሜሪካ በጣለችው የባህር ላይ እገዳ ሳቢያ ኢራን 4.8 ቢሊዮን ዶላር አጣች

በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትዕዛዝ በኦማን ባህረ ሰላጤ ላይ...

ኢሕአፓ ሊያካሂድ የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ ማራዘሙን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ሚያዚያ 30 ቀን 2018...

እሁድ መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ ይደረጋሉ

መነሻውንና መድረሻውን መስቀል አደባባይ የሚያደረገው ዓለም አቀፉ የዛይድ የበጎ...