7ኛው ምርጫ ትግራይን ጨምሮ በመላ የሀገሪቱ ይካሄዳል

Date:

ቀጣዩን ሰባተኛው ዙር ሀገር አቀፍ ምርጫ ትግራይ ክልልን ጨምሮ በሁሉም የሀገሪቱ አከባቢዎች ለማካሄድ ዝግጅቶች እየተከናወኑ መሆናቸውን ምርጫ ቦርድ አስታወቀ።

የቦርዱ ሰብሳቢ የሆኑት ሜላተወርቅ ኃይሉ ባሳለፍነው ሳምንት ሀሙስ ሐምሌ 10 ቀን 2017 ዓ.ም ተሻሽሎ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በጸደቀው “የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ” ዙርያ ለመገናኛ ብዙኃን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።

ከነባሩ አዋጅ ውስጥ 26ቱ ድንጋጌዎች ላይ ማሻሻያ መደረጉን ያስታወቁት ሰብሳቢዋ፤ አያይዘውም በሰባተኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ተግባራዊ ለማድረግ እና የወጣቶች እንዲሁም የሴቶች ተሳትፎን በሚያረጋግጥ መልኩ መሻሻሉን ጠቁመዋል።

ችግሮች ሲፈጠሩም የፓርቲዎች፣ የምርጫ ቦርድ እና የገዢው ፓርቲ አባላት የሚገኙበት የሶስትዮሽ ኮሚቴ ተቋቁሞ በውይይት እንዲፈታ በመደረግ ላይ መሆኑንም አክለዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከባድ ሙስና የተከሰሱትን 4 ተከሳሾችን፤ ፖሊስ ፍርድ ቤት ማቅረብ ሳይችል ቀረ

በከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸው በፖሊስ የ'ይፈለጋሉ" ማስታወቂያ የወጣባቸው...

ስለመካከለኛው ምስራቅ አዲስ ውጥረት እስካሁን የታወቁ ጉዳዮች

🔸 ትላንት ምሽት ከኢራን ግዛት የተተኮሰ የሮኬት ጥቃት በሰሜናዊ...

የወንጀል ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕጉ በጋዜጣ እስኪታተም ረቂቅ ሰነዶችን ከመጠቀም እንዲቆጠብ የፍትሕ ሚኒስቴር አሳሰበ

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የፍትሕ ሚኒስቴር አዲሱ የወንጀል ሕግ ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕግ...

ፔንታጎን የእስራኤል ስለላ እንደሚያሳስበው ተገለጸ

ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ ፔንታጎን እስራኤል ከፍተኛ ልዑኮችን ጨምሮ የአሜሪካ...