አቶ ቴዎድሮስ የአፍሪካ የጠበቆች ማህበራት ህብረት ፕሬዚደንት ሆነው ተመረጡ!

Date:

ኢትዮጵያዊው የህግ ባለሙያ አቶ ቴዎድሮስ ጌታቸው የአፍሪካ የጠበቆች ማህበራት ህብረት (PALU) ፕሬዚደንት ሆነው ተመረጡ።

ይህ ምርጫ በአቢጃን፣ አይቮሪ ኮስት እየተካሄደ ባለው 15ኛው የPALU መደበኛ ጉባኤ ላይ የተከናወነ ሲሆን፣ አቶ ቴዎድሮስ የምስራቅ አፍሪካን ክልል ወክለው ይህን ትልቅ የአህጉር አቀፍ ተቋም ለመምራት የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ እና የመጀመሪያው የምስራቅ አፍሪካዊ ዜጋ መሆናቸው ተጠቁሟል።

54 የአፍሪካ ሀገራት የጠበቆች ማህበራትን እና 8 አካባቢያዊ ተቋማትን በአባልነት የያዘው PALU፣ በአፍሪካ ውስጥ ካሉት ግዙፍ እና ቀዳሚ የህግ ተቋማት አንዱ ነው። አቶ ቴዎድሮስ ከሰጡት ድምጽ ውስጥ ከ3/4ኛ በላይ ድምጽ በማግኘት በቀጣዮቹ ሶስት ዓመታት ድርጅቱን ይመራሉ ተብሏል።

በመጨረሻው ዙር ምርጫ የተፎካካሪያቸው አልጄሪያዊቷ ወ/ሮ አይሻ ቡዳይፍ፣ የPALU የሰሜን አፍሪካ ምክትል ፕሬዚደንት የነበሩ ሲሆን፣ ከ1/3ኛው የአባል ሀገራት ድምጽ በማግኘት ተሸንፈዋል።

አቶ ቴዎድሮስ ለሦስት ዓመታት ያህል ተቋሙን በመምራት ላይ የነበሩትን ካሜሩናዊውን ሚስተር ካሪ አብዱልባጎይን ይተካሉ።

ከፕሬዚደንታዊ ምርጫው በተጨማሪ፣ ጉባኤው አምስት ምክትል ፕሬዚደንቶችን (የምስራቅ፣ ምዕራብ፣ መካከለኛው፣ ሰሜን እና ደቡብ አፍሪካ ክልሎችን የሚመሩ)፣ የድርጅቱ ዋና ፀሐፊን እና ዘጠኝ ሌሎች የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላትን መርጧል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...