በአክሱም ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ፈተና አልተፈተኑም

Date:

በትግራይ ክልልል ማእከላዊ ዞን አክሱም ከተማ የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ከሂጃብ ጋር በተያያዘ እንዳይፈተኑ ተደረጉ፡፡ ተማሪዎቹ ከዚህ በፊት በሂጃብ ምክንያት ከትምህርት ገበታ ውጭ ሆነው መቆየታቸው ይታወቃል፡፡

ለ8 ወራት ያህል ከትምህርት ተገልለው የቆዩትን እነዚህን ተማሪዎች በተመለከተ የትምህርት ሚኒስቴር በሰጠው መግለጫ የ12ተኛ ክፍል የዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተናን እንዲፈተኑ ፎርም ማስሞላቱን ማስታወቁ አይዘነጋም፡፡ ይሁን እንጂ ዛሬ በተጀመረውና በአክሱም ከተማም እየጠሰጠ ባለው በዚህ ፈተና ላይ እነዚህ ተማሪዎች እንዳይፈተኑ ተደርገዋል፡፡

የትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ በጉዳዩ ላይ በሰጠው አስተያየት የእነዚህ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች አድሚሽን ካርድ ዘግይቶ የደረሰው በመሆኑ በሁለተኛው ዙር እንዲፈተኑ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ገልጿል፡፡ የክልሉ የትምህርት ቢሮ ሀላፊ ዶክተር ኪሮስ ይህንን የሚገልፅ ሀሳብ በትግርኛ በማህበራዊ ገፃቸው ላይ ፅፈዋል፡

በመጪው ሀሙስ በሚጀመረው ሁለተኛ ዙር ፈተና ላይ እነዚህን ተማሪዎች ለማስፈተን ጥረት እንደሚያደርጉም አስረድተዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ በአክሱም ከተማ ከዚህ ቀደም ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ከሂጃብ ጋር በተያያዘ ምክንያት የ8ተኛ ክፍል ፈተናን ሳይፈተኑ መቅረታቸው ይታወሳል፡፡

(ዘ-ሐበሻ)

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...