ኤርትራ የአውሮፓ ህብረትን ወነጀለች

Date:

የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስትር አቶ የማነ ገብረ መስቀል፣ የአውሮፓ ኅብረት ሀገራቸውን “ለመቅጣት”  የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብቶች ምክር ቤትን “እንደ መሣሪያ” እንደሚጠቀም ከሰሱ።

ሚኒስትሩ ዋና መቀመጫውን በጄኔቭ ያደረገውን የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብቶች ምክር ቤት፣ “እየከሰመ ያለ ዓለም አቀፍ ሥርዓት ቅሪት” ሲሉ አጣጥለውታል፡፡

“ለራሳቸው የሞራል ልዕልና ያጎናጸፉ” ያሏቸው “የተወሰኑ” ልዕለ-ኃያላን፣ ለትዕዛዞቻቸው “የማይንበረከኩትን ለመቅጣት”፣ የተመድ የሰብአዊ መብቶች ምክር ቤትን እንደ መሣሪያ ይጠቀማሉ ሲሉ አቶ የማነ በኤክስ ባሰፈሩት መልክት ወንጅለዋል።

አቶ የማነ የአውሮፓ ኅብረትን  የወነጀሉት መንግሥታቸው በኤርትራ ተፈጽመዋል የተባሉ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችን ለመመርመር በተባበሩት መንግሥታት የሚሾሙ ባለሙያ ሥልጣን እንዲያበቃ ያቀረበው ጥያቄ ውድቅ በተደረገ ማግስት  ነው። 

DW Amharic

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...