ሊባኖስ በእስራኤል ጦር ተመታች

Date:

እስራኤል በበርካታ የሊባኖስ አካባቢዎች ላይ ከባድ የአየር ጥቃት ሰነዘረች።

የእስራኤል አየር ሀይል  በመላ ሊባኖስ ጥቃት ማደረሱን ከቤይሩት የሚወጡ መረጃዎች ያሳያሉ።

ተዋጊ ጀቶቹ በቦዳኢ ከተማ በምስራቃዊ ሊባኖስ  ቢያንስ ሶስት ጥቃት ማድረሳቸው ተነግሯል።

ከባዓ’ልቤክ ባሻገር ተጨማሪ ሶስት ጥቃቶች በአርዚ እና ቡርጅ ራሃል ከተሞች በደቡባዊ ሊባኖስ ደርሰዋል፡፡

በሊታኒ ወንዝ እና በሌሎች በርካታ የደቡባዊ ሊባኖስ ክፍሎች ከባድ የአየር ጥቃት መፈጸሙን የቤይሩት ምንጮች አረጋግጠዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ከጋዛ ወደ እስራኤል ሮኬት መወንጨፉ ተሰምቷል።

የእስራኤል ጦር ሮኬቱ በኪቡትዝ አቅራቢያ መውደቁን አረጋግጣል፡፡

የሃማስ ክንፍ  ቃሳም ብርጌድ በራጁም ሮኬቶች እስራኤል ላይ ጥቃት አድርሻለሁ ብሏል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመረጃ ነጻነት አዋጅን በሙሉ ድምፅ አጸደቀ

በምክር ቤቱ የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ እውነቱ...

በቬንዝዌላ በደረሰ የመሬት መንቀጥቀጥ የ32 ሰዎች ህይወት አልፏል

በቬንዙዌላ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የታወጀ ሲሆን 7.2 እና 7.5...

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ “ሉሲ” ላገኟት ፕሮፌሰር የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሰጠ

የዩኒቨርሲቲው ሴኔት ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ፥...

የሳህለወርቅ ዘውዴ አዲሱ አለም አቀፍ ሹመት በተመድ ልዩ ተልእኮ ተሰጣቸው

የቀድሞዋ የኢትዮጵያ ፕሬዝደንት ወይዘሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ በተመድ ዋና ፀሀፊ...