ዛሬ ምድር በከፍተኛ ፍጥነት እየዞረች መሆኑን የገለጹት ሳይንቲስቶች፤ ቀኑ አጭሩ ሊሆን እንደሚችልም ጠቁመዋል።
በዛሬው እለት ምድር በከፍተኛ ፍጥነት እየዞረች ነው ያሉት ሳይንቲስቶቹ፤እ ሽክርክሪቱ ከበፊቱ በበለጠ ፍጥነት የሚካሄድ በመሆኑ ዛሬ ጁላይ 9 ቀን 2025 ዓ.ም በሰው ልጆች ታሪክ አጭር ቀን ሊሆን እንደሚችል አብራርተዋል።
በዚህም ዛሬን ጨምሮ በፈረንጆቹ ጁላይ 22 እና ኦገስት 5 ቀናቶቹ ከወትሮው በ1 ነጥብ 3 እና 1 ነጥብ 51 ሚሊ ሰከንዶች የሚያጥሩ እንደሚሆኑ ዴይሊ ሜል ዘግቧል፡፡
ዘገባዎች እንደሚያሳዩት፤ ይኼ ክስተት እ.ኤ.አ ከ2020 ጀምሮ የተስተዋለ ሲሆን፤ ጁን 5 ቀን 2024 ዓ.ም ከወትሮው በ1.66 ሚሊ ሰከንዶች ያጠረ ቀን መከሰቱ ተመዝግቧል፡፡
የክስተቱ ምክንያት አሁንም ድረስ በሳይንቲስቶች እየተጠና ነው ተብሏል፡፡
