አስካሪ ሜታልስ በኢትዮጵያ ግዙፍ የወርቅ ፕሮጀክት ገዛ

Date:

አውስትራሊያዊው የአክሲዮን ኩባንያ አስካሪ ሜታልስ በኢትዮጵያ የሚገኘውን ትልቅ የኒጆ ወርቅ ፕሮጀክት ለመግዛት ስምምነት ላይ መድረሱን አስታወቀ። ግዢው ኩባንያው በኢትዮጵያ የማዕድን ኢንዱስትሪ ውስጥ ትልቅ ድርሻ እንዲይዝ የሚያስችለው ሲሆን፣ ፕሮጀክቱ 1,174 ካሬ ኪሎ ሜትር ስፋት አለው።

ይህ የተፈፀመው ደግሞ የፕሮጀክቱ ባለቤት ከነበረው ዢንግሹ ማይኒንግ ኢንተርናሽናል ኢንቨስትመንት የተባለውን ኩባንያ ላይ 100% ድርሻ በመግዛት ነው።

ይህ ግዢ አስካሪ ሜታልስ ባለፉት 4 ዓመታት በኢትዮጵያውያን አጋሮች ሲስተዳደር የነበረውን የኒጆ ፕሮጀክት ላይ ሙሉ ህጋዊ እና የባለቤትነት መብትን የሚያስገኝለት ይሆናል ተብሏል።

የኒጆ ፕሮጀክት በአረቢያ-ኑቢያን ጋሻ ውስጥ የሚገኝ ሲሆን፣ ይህ የበለፀገ የጂኦሎጂካል ክልል በግብፅ፣ ሱዳን፣ ኤርትራ፣ ኢትዮጵያ፣ ሳውዲ አረቢያ እና የመን በሚገኙ በርካታ ሚሊዮን አውንስ የወርቅ ክምችቶች ይታወቃል።

የኒጆ የወርቅ ፕሮጀክት እንደ ካናዳዊው ማዕድን አውጪ አላይድ ጎልድ ባለቤትነት ስር ያለው የ3.4 ሚሊዮን አውንስ የኩርሙክ ማዕድን ማውጫ እና የኬፊ ጎልድ ኤንድ ኮፐር ባለቤትነት ስር ያለውን የ1.7 ሚሊዮን አውንስ ቱሉ ካፒ ማዕድን ማውጫ በሚያዋስነው ተመሳሳይ የግሪን ስቶን ቤልት ላይ ይገኛል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ጥቃት አድራሹ ከካሊፎርኒያ መሆኑን ትራፕ ገለፁ

ትናንት ቅዳሜ ምሽት በዋይት ሃውስ የጋዜጠኞች ማኅበር የእራት ግብዣ...

በኬንያ የመንገደኞች አውሮፕላን ከመስመሩ ወጥቶ ተከሰከሰ

ዛሬ ረፋድ ላይ በኬንያ ማንዴራ የአውሮፕላን ማረፊያ አንድ...

አቶ ጀማል አህመድ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ተጨማሪ 26 ሚሊየን ብር ሰጡ

አቶ ጀማል አህመድ ባሳለፍነው ወር ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ  ከሰጠው...

“የቻይና-አፍሪካ የምርምር ማዕከል”በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሊከፈት ነው

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከቻይና-አፍሪካ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር "የቻይና-አፍሪካ የምርምር...