በቂ የሙያ ስልጠና ባለመሰጠቱ በሠራተኞች ላይ አደጋ እየደረሰ ነው

Date:

ለሠራተኞች የሙያ ስልጠና ሳይሰጥ ወደ ሥራ እንዲሰማሩ መደረጋቸው ለአደጋ ተጋላጭ እንዲሆኑ እያደረጋቸው እንደሚገኝ የኢትጵያ ሠራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን አስታውቋል፡፡

በተለያዩ የሥራ መስኮች ላይ በተሰማሩ ሠራተኞች ስለ ሚሰሩት የሥራ መስክ በቂ የሆነ የሙያ ስልጠና እንዲሰጣቸው ማድረግ ከተቋማት የሚጠበቅ ኃላፊነት የሚጠበቅ መሆኑን የተናገሩት በኮንፌዴሪሽኑ የውጭ እና የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ አያሌው አህመድ ናቸው፡፡

በተደጋጋሚ ሠራተኞች የተለያየ ጉዳት እየደረሰባቸው መሆኑን አንስተው፤ የሥራ ቦታቸው ከኬሚካል ጋር ግንኙነት ባላቸው ሠራተኞች ለጉዳቱ የበለጠ ተጋላጭ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

የሥራ የደህንነት መስፈርቶች ባለመሟላታቸው የሚደርሱ ጉዳቶች በዜጎችን ሕይወት ላይ ጫና እያሳደረ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው፤ ሠራተኞች የሥራ ላይ ደህንነትን በተሟላ ሁኔታ ባለመከተላቸው ምክንያት ሕወታቸው እያለፈ እና ለአካል ጉዳት እየተዳረጉ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

በሥራ ቦታ ላይ ያለው የሥራ ደህንነት መስፈር በተመለከተ ክትትል የማያካሄድ ኃላፊነት ያለው የሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ቢሆንም፤ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ችግሩን በብቸኝነት ሊፈታ ባለመቻሉ ሁሉም ባለ ድርሻ የበኩሉን ኃላፊነት ሊወጣ እንደሚገባ አሳስበዋል ።


ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኔታንያሁ እና ትራምፕ የፊታችን ማክሰኞ በዋይት ሀውስ እንደሚወያዩ ተገለጸ

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፤ ቤንያሚን ኔታንያሁ ከፕሬዝዳንት ዶናልድ...

አሜሪካ በኢትዮጵያ ያላትን የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር ለማጠናከር ከኢትዮጵያ መንግሥትና ከግሉ ዘርፍ ጋር ውይይት አካሄደች

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ጄ. ማሲንጋ፣ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን...

የካፍ ፕሬዝዳንት የ2027 አፍሪካ ዋንጫ በ24 ተሳታፊ ሀገራት እንደሚካሄድ አስታወቁ

የአፍሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (ካፍ) ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሙትሰፔ የ2027...

የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ነፃ የጤና ምርመራና ሕክምና መስጠት ጀመረ

ሆስፒታሉ በቀን ከ300 በላይ ታካሚዎችን ያስተናግዳል የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከሐምሌ...