የ2018 በጀት ዓመት 350.13 ቢሊዮን ብር ሆኖ ጸደቀ !!

Date:

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 በጀት ዓመት 350.13 ቢሊዮን ብር ሆኖ በአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት በሙሉ ድምፅ ፀደቀ።

ይህ በጀት ካለፈው የበጀት ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ108 ቢሊዮን ብር ወይም የ45 በመቶ ዕድገት ያሳየ መሆኑን በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ የሆኑት አቶ አብዱል ቃድር ሬድዋን አስታውቀዋል።

አቶ አብዱል ቃድር ሬድዋን የበጀት ረቂቅ አዋጁን ለምክር ቤቱ ባቀረቡበት ወቅት፣ በጀቱ የሚሸፈንባቸውን ዋና ዋና የፋይናንስ ምንጮች ዘርዝረዋል።

በዚህም መሰረት፡-

  • ከታክስ ከ238 ቢሊዮን ብር በላይ ወይም 68 በመቶ
  • ከማዘጋጃ ቤታዊ ገቢ ከ56 ቢሊዮን ብር በላይ
  • ታክስ ካልሆነ ገቢ ከ46 ቢሊዮን ብር በላይ
  • ከመንገድ ፈንድ 1.8 ቢሊዮን ብር
  • ከውጭ ብድርና እርዳታ ደግሞ 6.98 ቢሊዮን ብር እንደሚገኝ ተገልጿል።

ከፀደቀው አጠቃላይ በጀት ውስጥ፣ 70.35 በመቶ ለካፒታል በጀት፣ 26.22 በመቶ ለመደበኛ በጀት እንዲሁም 3.43 በመቶ ለመጠባበቂያነት መያዙ ታውቋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...

ትራምፕ ኢራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት እየተሟጠጠ መሆኑን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ ጋር...