የቻይናን የጥቃት ስልቶችን ለመመከት በሚል በታይዋን ጁላይ 9 በይፋ የጀመረው ዓመታዊ የሃን ኩዋንግ ወታደራዊ ልምምድ የታላቁ ታይፔ አካባቢ ቁልፍ የሆነዉን ድልድይ ሙሉ ለሙሉ መዝጋቱን እና የከተማው ነዋሪዎች ላይ የእንቅስቃሴ ገደብ መጣሉ ተሰማ ።
የጠላት ኃይሎች ወደ ታይፔ እንዳይገቡ ለመከላከል የታሰቡ በተባሉት “ግራጫ ቀጠና” የሚል ስያሜ በተሰጠዉ ስልጠናዎች አላማቸዉ የፕሬዚዳንቱ ጽሕፈት ቤት ሕንፃ፣ የታይፔ ዋና ጣቢያ እና ሌሎች ቁልፍ ቦታዎች መከላከል የሚያስችሉ እንደሆነ ያሳወቀዉ የታይዋን ጦር የኒው ታይፔ ባንኪያኦ ዲስትሪክት ከታይፔ ዋንዋ ዲስትሪክት ጋር የሚያገናኘው የዋንባን ድልድይ
ልምምዱን ለማቀላጠፍ በሚል ሙሉ ለሙሉ መዘጋቱ ተገልጿል ።
እንደ ታይዋን ትሪቡን የዜና አገልግሎት ዘገባ ከሆነ የቻይና ሃይሎች ወደ ዋና ከተማዋ እንዳይንቀሳቀሱ ለማስቆም ያስችላሉ በተባሉት ልምምዶች ወታደሮች በሁለት ሰአታት ውስጥ በ690 ሜትር ርቀት ላይ ባለ አራት እርከን እገዳን ገንብተዋል ።
ቻይና ከሰሞኑ በታይዋን ዙሪያ የተቀናጀ የጦር ልምምድ ማድረጓን ተከትሎ ታይዋን የወታደራዊ ልምምድ ማድረግ ጀምራለች።
ቻይና ከአሜሪካ ጋር በታይዋን ዙሪያ ወደ ውጊያ ሊገቡ እንደሚችሉ የቻይና ሚዲያዎች ዘግበዋል።
