ኮካ ኮላ ባቀረብኩት ሃሳብ ተስማምቷል – ትራምፕ

Date:

የኮካ ኮላ ኩባንያ በአሜሪካ የኮላ ምርት ውስጥ እውነተኛ የሸንኮራ አገዳ ስኳር እንዲጠቀም እንዳሳመኑት ፕሬዚዳንት ትራምፕ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል፡፡

“ይህ በጣም ጥሩ እርምጃ ነው” ሲሉም ኩባንያውን አመስግነዋል፡፡

የዳይት ኮክ አድናቂ የሆኑት ትራምፕ፤ ከኮካ ኮላ ጋር መነጋገራቸውን ጠቁመው፤ ባቀረቡት ሃሳብ ኩባንያው መስማማቱን ገልጸዋል፡፡

ኮካ ኮላ ለሲቢኤስ ኒውስ በላከው ኢሜል፤ “ፕሬዚዳንት ትራምፕ ለታዋቂው የኮካ ኮላ ብራንድ ያሳዩትን ጉጉት እናደንቃለን። በኮካ ኮላ ምርት ውስጥ ያሉ አዳዲስ ፈጠራዎችን በተመለከተ ተጨማሪ ዝርዝሮች በቅርቡ ይጋራሉ።” ብሏል፡፡

ኮካ ኮላ ከአሜሪካ ውጭ በተለይም በሜክሲኮ የኮላ መጠጡን የሚያመርተው በሸንኮራ አገዳ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ በአሜሪካ ግን መጠጡ ከፍተኛ-ፍሩክቶስ ባለው የበቆሎ ሲሮፕ የሚሰራ እንደሆነ በኮካኮላ ድረገጽ ላይ የሰፈረው መረጃ ይጠቁማል፡፡

“በኮካ ኮላ ኩባንያ ውስጥ ያሉትን ሃላፊዎች በሙሉ ማመስገን እፈልጋለሁ። በጣም ጥሩ እርምጃ ነው የወሰዱት፡፡ ታያላችሁ – የተሻለ ነው!” ሲሉ ትራምፕ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ አስፍረዋል፡፡

ትላንት ረቡዕ የኮካ ኮላ አክሲዮን ሽያጭ፣ በ9 ሳንቲም ወይም 0.13 በመቶ በመቀነስ ወደ 69.27 ዶላር ዝቅ ማለቱ ተዘግቧል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኔታንያሁ እና ትራምፕ የፊታችን ማክሰኞ በዋይት ሀውስ እንደሚወያዩ ተገለጸ

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፤ ቤንያሚን ኔታንያሁ ከፕሬዝዳንት ዶናልድ...

አሜሪካ በኢትዮጵያ ያላትን የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር ለማጠናከር ከኢትዮጵያ መንግሥትና ከግሉ ዘርፍ ጋር ውይይት አካሄደች

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ጄ. ማሲንጋ፣ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን...

የካፍ ፕሬዝዳንት የ2027 አፍሪካ ዋንጫ በ24 ተሳታፊ ሀገራት እንደሚካሄድ አስታወቁ

የአፍሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (ካፍ) ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሙትሰፔ የ2027...

የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ነፃ የጤና ምርመራና ሕክምና መስጠት ጀመረ

ሆስፒታሉ በቀን ከ300 በላይ ታካሚዎችን ያስተናግዳል የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከሐምሌ...