በዩኤስ ኤይድ መዘጋት የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የበጀት ችግር አጋጠማችው

Date:

የአሜሪካው የተራድኦ ድርጅት ዩኤስኤይድ መዘጋቱን ተከትሎ በርካታ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የበጀት ችግር እንዳጋጠማቸው ተነግሯል።

ለአውሮፓውያኑ 2025 ይዘን ከነበረው በጀት ውስጥ 14 በመቶ ያህሉ በዩኤስኤይድ ድጋፍ መቋረጥ ምክንያት ተጽዕኖ ውስጥ ገብቷል ያሉት የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች ሕብረት ዋና ዳይሬክተር አቶ መስዑድ ገበየሁ፤ የተጓደለውን በጀት ለማሟላት የተለያዩ እንቅስቃሴዎችን ማድረጋቸውን ጠቁመዋል።

በድርጅቱ ድጋፍ ተጀምረው የነበሩ ፕሮጀክቶች መቋረጣቸውን አክለው የገለጹት ዋና ዳይሬክተሩ፤ የበጀት ጉድለቱን ለመቅረፍ ያካሄዱት እንቅስቃሴ ፍሬ ማፍራቱን ገልጸዋል።

በዚህም አሁን ላይ ህብረቱ በጀቱን ማሟላት መቻሉን ገልጸዋል። ሌሎች በርካታ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በመሰል ፈተና ውስጥ መሆናቸውንም የጠቆሙት አቶ መስዑድ፤ በሀገር ውስጥ ድጋፍ ማግኘት የሚቻልበትን መንገድ በማፈላለግ ዘላቂ መፍትሄ ማበጀት እንደሚገባ አመልክተዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ጥቃት አድራሹ ከካሊፎርኒያ መሆኑን ትራፕ ገለፁ

ትናንት ቅዳሜ ምሽት በዋይት ሃውስ የጋዜጠኞች ማኅበር የእራት ግብዣ...

በኬንያ የመንገደኞች አውሮፕላን ከመስመሩ ወጥቶ ተከሰከሰ

ዛሬ ረፋድ ላይ በኬንያ ማንዴራ የአውሮፕላን ማረፊያ አንድ...

አቶ ጀማል አህመድ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ተጨማሪ 26 ሚሊየን ብር ሰጡ

አቶ ጀማል አህመድ ባሳለፍነው ወር ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ  ከሰጠው...

“የቻይና-አፍሪካ የምርምር ማዕከል”በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሊከፈት ነው

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከቻይና-አፍሪካ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር "የቻይና-አፍሪካ የምርምር...