ለመቄዶንያ ከ13 ሚ. ብር በላይ የሚያወጡ የሕክምና መሣሪያዎች ተሰጡ

Date:

የአማራ ልማት ማኅበር (አልማ)፤ ለመቄዶንያ የአረጋዊያንና የአዕምሮ ሕሙማን ማዕከል ከ13 ሚሊዮን በላይ ብር የሚያወጡ የተለያዩ የሕክምና መሣሪያዎችን ዛሬ አስረክቧል።

የተደረገው ድጋፍ ወደ ማዕከሉ የሚመጡ ወገኖችን ጤና ከመጠበቅ ባሻገር በማዕከሉ የተጠለሉ ወገኖችን ሕይወትን  የሚያሻሽል መኾኑን ተጠቃሚዎች ተናግረዋል።

ድጋፉ በሕክምና መሳሪያዎች እጥረት ይገጥማቸው የነበረውን ችግር በመፍታት በኩል ሚናው የላቀ መኾኑን በመቄዶንያ አረጋዊያንና አዕምሮ ሕሙማን ማዕከል የሚገኙ አረጋዊያን ገልጸዋል።

የመቄዶንያ ማኅበር መሥራች ቢኒያም በለጠ ተወካይ አቶ አሰፋ ባለሄር በበኩላቸው፤ አልማ ያደረገው የሕክምና ቁሳቁስ ድጋፍ የማዕከሉን የዕለት ተዕለት አገልግሎት አሰጣጥ የሚያሻሽል መኾኑን ገልጸዋል።

አልማ የዛሬውን ጨምሮ ከዚህ ቀደም የ17 ሚሊዮን ብር አልባሳትና ሌሎች ድጋፎችን በሦስት ዙሮች ማድረጉ ተገልጿል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኔታንያሁ እና ትራምፕ የፊታችን ማክሰኞ በዋይት ሀውስ እንደሚወያዩ ተገለጸ

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፤ ቤንያሚን ኔታንያሁ ከፕሬዝዳንት ዶናልድ...

አሜሪካ በኢትዮጵያ ያላትን የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር ለማጠናከር ከኢትዮጵያ መንግሥትና ከግሉ ዘርፍ ጋር ውይይት አካሄደች

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ጄ. ማሲንጋ፣ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን...

የካፍ ፕሬዝዳንት የ2027 አፍሪካ ዋንጫ በ24 ተሳታፊ ሀገራት እንደሚካሄድ አስታወቁ

የአፍሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (ካፍ) ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሙትሰፔ የ2027...

የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ነፃ የጤና ምርመራና ሕክምና መስጠት ጀመረ

ሆስፒታሉ በቀን ከ300 በላይ ታካሚዎችን ያስተናግዳል የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከሐምሌ...