የቀድሞ ፕሬዚዳንት የሰላም ሂደት እንዲያስተባብሩ ተመረጡ

Date:

የቀድሞዋ የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት ሣሕለወርቅ ዘውዴ፣ የኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክን የሰላም ሂደት እንዲያስተባብሩ  ተመረጡ፡፡

የዚምባብዌ መሪ የምሥራቅ ኮንጎ ግጭት ዋና መንስኤ መፍትሄ እንዲያገኝ  ጥሪ አቅርበዋል፡፡

የደቡብ አፍሪካ የልማት ማኅበረሰብ ሊቀመንበር ፕሬዚዳንት ኤመርሰን ምናንጋግዋ፤ ከምሥራቅ አፍሪካ ማኅበረሰብ ሊቀመንበር የኬንያ ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ ጋር በመሩት የቨርቹዋል ጉባኤ ላይ ነው ጥሪውን ያቀረቡት፡፡

“ክቡራን፤ እህት ሀገር ኮንጎ ዴሞክራሲያው ሪፐብሊክ ያጋጠሟትን ፈተናዎች ለመፍታት በጋራ ባለን ቁርጠኝነት ላይ ለመሳተፍ ጊዜ ስለሰጣችሁን አመሰግናለሁ” ሲሉ ምናንጋግዋ ለአፍሪካ መሪዎች ተናግረዋል፡፡

ጉባኤው አምስት የቀድሞ የአፍሪካ ፕሬዚዳንቶችን በአስተባባሪነት በይፋ ሾሟል፡፡

ኦሉሴጉን ኦባሳንጆ (ናይጄሪያ)

ኡሁሩ ኬንያታ (ኬንያ)

ካትሪኔ ሳምባ-ፓንዛ (ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ)

ሣሕለወርቅ ዘውዴ (ኢትዮጵያ)

ሞክግዌትሲ ማሲሲ (ቦትስዋና)

ምናንጋግዋ እና ሩቶ፤ የደቡብ አፍሪካ የልማት ማኅበረሰብ (የሉዋንዳ) እና የምሥራቅ አፍሪካ ማኅበረሰብ (የኬንያ) የተናጠል የሰላም ሂደቶች ወደ አንድ አፍሪካ መር ተነሳሽነት እንዲዋሃዱ ወስነዋል፡፡

Sputnik-

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...