የቀድሞ ፕሬዚዳንት የሰላም ሂደት እንዲያስተባብሩ ተመረጡ

Date:

የቀድሞዋ የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት ሣሕለወርቅ ዘውዴ፣ የኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክን የሰላም ሂደት እንዲያስተባብሩ  ተመረጡ፡፡

የዚምባብዌ መሪ የምሥራቅ ኮንጎ ግጭት ዋና መንስኤ መፍትሄ እንዲያገኝ  ጥሪ አቅርበዋል፡፡

የደቡብ አፍሪካ የልማት ማኅበረሰብ ሊቀመንበር ፕሬዚዳንት ኤመርሰን ምናንጋግዋ፤ ከምሥራቅ አፍሪካ ማኅበረሰብ ሊቀመንበር የኬንያ ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ ጋር በመሩት የቨርቹዋል ጉባኤ ላይ ነው ጥሪውን ያቀረቡት፡፡

“ክቡራን፤ እህት ሀገር ኮንጎ ዴሞክራሲያው ሪፐብሊክ ያጋጠሟትን ፈተናዎች ለመፍታት በጋራ ባለን ቁርጠኝነት ላይ ለመሳተፍ ጊዜ ስለሰጣችሁን አመሰግናለሁ” ሲሉ ምናንጋግዋ ለአፍሪካ መሪዎች ተናግረዋል፡፡

ጉባኤው አምስት የቀድሞ የአፍሪካ ፕሬዚዳንቶችን በአስተባባሪነት በይፋ ሾሟል፡፡

ኦሉሴጉን ኦባሳንጆ (ናይጄሪያ)

ኡሁሩ ኬንያታ (ኬንያ)

ካትሪኔ ሳምባ-ፓንዛ (ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ)

ሣሕለወርቅ ዘውዴ (ኢትዮጵያ)

ሞክግዌትሲ ማሲሲ (ቦትስዋና)

ምናንጋግዋ እና ሩቶ፤ የደቡብ አፍሪካ የልማት ማኅበረሰብ (የሉዋንዳ) እና የምሥራቅ አፍሪካ ማኅበረሰብ (የኬንያ) የተናጠል የሰላም ሂደቶች ወደ አንድ አፍሪካ መር ተነሳሽነት እንዲዋሃዱ ወስነዋል፡፡

Sputnik-

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...

ትራምፕ ኢራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት እየተሟጠጠ መሆኑን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ ጋር...