ግብፅ ለኤርትራ የሕክምና ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገች

Date:

የሕክምና ቁሳቁስ የያዘ የግብፅ አውሮፕላን ባሳለፍነው ዓርብ ነሐሴ 23 ቀን 2017 ዓ.ም. አስመራ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ መደረሱን የግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።

ለኤርትራ የመድሃኒት አስተዳደር የተበረከተው ይህ እርዳታ፣ የዓይን ህክም እና የኩላሊት እጥበት መስሪያ ቁሳቁሶችን ያካተተ ነው። እርዳታው የቀረበው በግብፅ የልማት አጋርነት ኤጀንሲ አማካይነት መሆኑ ተመላክቷል።

እንደ ሚኒስቴሩ ገለፃ፤ ይህ ድጋፍ ካይሮ ከኤርትራ ጋር ያላትን “ስትራቴጂያዊና እህትማማች ወዳጅነትን” ለማጠናከር የምታደርጋቸው ጥረቶች አካል ነው።

የህክምና ቁሳቁስ እርዳታው ወደ አስመራ የተላከው፣ የግብፁ ፕሬዚዳንት አብዱልፈታህ አል ሲሲ ጥቅምት ወር በአስመራ ያደረጉትን ጉብኝት ተከትሎ ነው። ጉበኝቱ የሁለቱን ሀገራት የሁለትዮሽ ትብብር አዲስ ምዕራፍ መሆኑን ሁለቱም ሀገራት ገልፀዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...