የዓረብ ሊግ የውጭ ጉዳይ ሚንስትሮች፣ ኢትዮጵያ፣ ግብጽና ሱዳን በሕዳሴ ግድብ የውሃ ሙሌትና አስተዳደር ዙሪያ ባስቸኳይ አስገዳጅ የሦስትዮሽ ስምምነት ላይ እንዲደርሱ ካይሮ ውስጥ ከተሰበሰቡ በኋላ ባወጡት የጋራ መግለጫ አሳስበዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚንስትሮቹ፣ ስምምነቱ የግብጽንና ሱዳንን የውሃ ደኅንነት የሚያረጋግጥ መኾን እንዳለበትም ገልጸዋል።
የግብጽና ሱዳንን የውሃ መብት የሚጥስ ማናቸውንም የተናጥል ርምጃ ውድቅ ያደረጉት የውጭ ጉዳይ ሚንስትሮቹ፣ አስገዳጁ የሦስትዮሽ ስምምነት የኹለቱን አገራት የውሃ ደኅንነት የሚያረጋግጥ መኾን አለበት በማለት አቋማቸውን ገልጸዋል።
ዓረብ ሊግ ሕዳሴ ግድብን ወደፊትም መወያያ አጀንዳው አድርጎ እንደሚቀጥልም ውጭ ጉዳይ ሚንስትሮቹ አስታውቀዋል።
[ዋዜማ]
