የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ወደ ተሟላ ኦንላይን ግብይት መግባቱን አስታወቀ

Date:

ባለፈው በጀት ዓመት የቀጥታ የበይነ መረብ ግብይት ስርዓት በመተግበር ነጋዴዎች ባሉብት ሆነው እንዲገበያዩ ሲሠራ የቆየው ምርት ገበያው፤ በዘንድሮው ዓመት የኦንላይን ግብይትን ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ ማድረግ መቻሉን የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ሥራ አስፈፃሚ አቶ መርጊያ ባይሳ ተናግረዋል።

የግብይት ሥርዓቱ መተግበር ከጀመረበት ከሚያዚያ ወር ጀምሮ 12.5 ቢሊዮን ብር ዋጋ የሚተመን 127 ሺህ 830 ሜትሪክ ቶን ምርት ማገበያየት መቻሉን ጠቁመዋል።

የግብርና ምርቶች ግብይት ሥርዓትን በማዘመን፣ ግልፀኝነትንና መተማመንን በመፍጠር በሀገሪቱ የኢኮኖሚ ስርዓት ውስጥ ጉልህ ሚና እንደሚኖረውም አስረድተዋል።

የኦንላይን የግብይት ሥርዓቱ ምቹ፣ አስተማማኝ፣ ቀልጣፋ፣ ከሰው ንክኪ ነፃ የሆነና ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ማድረግ የሚያስችል ነው መባሉን ከስፑትኒክ ሰምተናል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...