ማክሮን ከሥልጣን የለቀቁትን ጠቅላይ ሚኒስትር መልሰው ሾሙ

Date:

የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ከአራት ቀናት በፊት ሥልጣን የለቀቁትን ጠቅላይ ሚኒስትር ዳግመኛ ሾሙ።

የፈረንሳዩ ጠቅላይ ሚኒስትር ሰባስሽን ሌኮርኑ አንድ ወር ሳይሞላቸው ሥልጣን መልቀቃቸው ይታወሳል።

“ሥራውን አልፈልገውም፤ ኃላፊነቴን ጨርሻለሁ” ብለው ከሥልጣን የለቀቁት ሰባስሽን ሌኮርኑ ወደ ሥልጣን መመለሳቸው አነጋጋሪ ሆኗል።

በድጋሚ የተሾሙት ጠቅላይ ሚኒስትር እስከ ሰኞ ድረስ የቀጣዩን ዓመት በጀት ለፓርላማ ማቅረብ አለባቸው።

የ39 ዓመቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ከማክሮን ዋነኛ ደጋፊዎች አንዱ ናቸው።

በኤክስ ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት “ፕሬዝዳንቱ በሰጡኝ ኃላፊነት መሠረት የፈረንሳይን በጀት ከማቅረብ ባሻገር ፈረንሳውያን ለሚገጥሟቸው ችግሮች መፍትሔ አበጃለሁ” ብለዋል።

ባለፈው ሳምንት “ጠቅላይ ሚኒስትር ሆኜ ለመቀጠል የሚያስችል ሁኔታ አልተሟላም” ሲሉ ለሥልጣናቸው መልቀቅ ምክንያት የሆናቸውን መግለጻቸው ይታወሳል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...

ኧረ ፋታ ስጡን?!

መንግስት ግን" ምን ሁኑ ?" ሊለን ነው :: አጀንዳ...