የቀድሞው የኬንያ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ በ80 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን በቢሮአቸው ውስጥ ያለ ምንጭ ጠቅሶ ሮይተርስ ዛሬ ጠዋት ዘግቧል።
እስካሁን ተጨማሪ ዝርዝር ነገር አልተገለጸም።
በደቡብ ህንድ ኮቺ ከተማ ህክምና ሲከታተሉ የነበሩት ኦዲንጋ ዛሬ በልብ ድካም ምክንያት ህይወታቸው ማለፉን ተዘግቧል።
አንጋፋ ተቃዋሚ መሪ የሆኑት ኦዲንጋ ለኬንያ ፕሬዝዳንትነት አምስት ጊዜ ቢወዳደሩም አላሸነፉም። ከእነዚህ ምርጫዎች ውስጥ ሁለቱ — በፈረንጆቹ 2007 እና በ2017 የተደረጉት — ብጥብጥን በመቀስቀስ በአገሪቱ ውስጥ ወደ ሁከት እና ጥልቅ ክፍፍል አምርተዋል።
ኦዲንጋ በኬንያ ዲሞክራሲያዊ ለውጥ ውስጥ ባላቸው ሚና በሰፊው ይታወቃሉ።
