ለስንዴ አምራቾች ግዥ የሚፈጸም ክፍያ ላይ የነበረው የ2% ቅድመ ግብር ክፍያ ተነሳ

Date:

የገቢዎች ሚኒስቴር፣ የስንዴ ምርት አቀነባባሪ አምራቾች ለሚያደርጉት የስንዴ ግዥ የሚፈጸም ክፍያ ላይ የነበረው የ2% ቅድመ ግብር ክፍያ ሥርዓት ተፈጻሚ እንዳይሆን መወሰኑን አስታወቀ።

ይህ ውሳኔ የተላለፈው የስንዴ አቀነባባሪ አምራቾች በግዥ ወቅት ለሚከፍሉት ቅድመ ክፍያ፣ ታክስ ባለስልጣኑ ሻጮቹ ደረሰኝ መስጠት ስለማይገደዱ ግብይቱን ውድቅ በማድረግ ከፍተኛ ግብር እየጠየቀ ነው በሚል ለብሔራዊ ኢንዱስትሪው ካውንስል ባቀረቡት ጥያቄ መሠረት መሆኑ ተጠቁሟል።

ችግሩን ለመፍታት የተቋቋመው የጥናት ኮሚቴ ያቀረበው የውሳኔ ሀሳብ ተቀባይነት በማግኘቱ፣ የገንዘብ ሚኒስቴር ከወር በፊት በተጻፈ ደብዳቤ ውሳኔ አስተላልፏል።

ይህን ተከትሎ ለስንዴ ግዥ የሚፈጸም ክፍያ የቅድመ ግብር ክፍያ ሥርዓት ተፈጻሚ እንዳይሆን የተወሰነ ሲሆን ውሳኔውም በታክስ ውሳኔ ቅሬታ አጣሪ ጽ/ቤት በሂደት ላይ ባሉና በቀጣይ ኦዲት ሥራዎች ተፈጻሚ እንዲደረግ ታዟል።

የገቢዎች ሚኒስቴር ከሰሞኑ በላከዉ ሰርኩላር ላይ እንደተመላከተዉ ፤ የገንዘብ ሚኒስትር ዉሳኔ መሰረት በግዥ ማረጋገጫ የተፈጸመ ግብይት በሌሎች መረጃዎች እየተረጋገጠ ወጪውን የሚያዝበት ሥርዓት በታክስ ባለስልጣኑ በኩል እንዲዘረጋ አሳስቧል።

CapitalNews

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...