በአዲስ አበባ በጾታዊ ጥቃት የህክምና አገልግሎት ለማግኘት ከሚሄዱት መካከል ከ70 እስከ 80 በመቶ የሚሆኑት ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች ያሉ ልጆች ናቸው ተብሏል።
በአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ሴቶች ህጻናት ጉዳይ ዳይሬክተር ሄለን አዱኛን አናግሮ በሰራው ዘገባ በልጆች ላይ የሚደርሰው ጾታዊ ጥቃት እጅግ ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሷል።
ቢሮው ጥቃት ደርሶባቸው ህክምና ለማግኘት ከሚመጡት ተገልጋዮች ውስጥ 90 በመቶ የሚሆኑት ሴቶች 10 በመቶዎቹ ወንዶች መሆናቸውንም ዳሬክተሯ ተናግረዋል።
አክለውም፥ 60 በመቶ የሚሆኑት ጥቃት አድራሾች የተጠቂዎቹ የቅርብ ቤተሰብ ወይም በቅርብ ያሉ ሰዎች መሆናቸውን ጠቅሰው፥ 40 በመቶ የሚሆኑት ደግሞ የማያውቋቸው ሰዎች እንደሆኑ ነው የገለጹት።
ዘገባው ጥቃት ከደረሰባቸው መካከል በኤች አይ ቪ እና ሌሎች የአባላዛር በሽታዎች የተያዙ ተጠቂዎች ቁጥር አነስተኛ ቢሆንም በበሽታዎቹ መያዛቸው የታወቁ እንዳሉ ጠቅሷል።
አራዳ ኤፍ.ኤም
@TikvahethMagazine
