አሜሪካ እና ሩሲያ የዩክሬን ግጭት ለመፍታት በድብቅ አዲስ እቅድ እያወጡ ነዉ

Date:

የታቀደው ባለ 28 ነጥብ የአሜሪካ እቅድ በአራት ዋና ዋና ጭብጦች የተዋቀረ ነው። የዩክሬን ሰላም፣ የደህንነት ዋስትናዎች፣ የአውሮፓ ደኅንነት እና አሜሪካ ከሩሲያ እና ከዩክሬን ጋር ወደፊት በሚኖራት ግንኙነት ዙሪያ ሆነው መለየታቸውን የአሜሪካ ሚዲያ ዘግቧል።

እቅዱ ከትራምፕ “ስኬታማ” የጋዛ ስምምነት ጥረቶች ተነሳሽነት እንዳመጣም ተገልጿል።

እቅዱ አወዛጋቢ አካባቢዎችን እንዴት መፍትሄ እንደሚሰጣቸው ዝርዝር መረጃው ግልፅ አይደለም ሲል ዘገባው አክሏል።

የሩሲያ ከፍተኛ ባለሥልጣን በእቅዱ ላይ ያላቸውን ተስፋ የገለፁ ሲሆን የኪዬቭ እና የአውሮፓ አጋሮቿ ምላሽ እስካሁን አለመታወቁን ዘገባው አመልክቷል።

እቅዱን የመሩት የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ ስቲቭ ዊትኮፍ ከሩሲያ ፕሬዝዳንታዊ መልዕክተኛ ኪሪል ዲሚትሪቭ ጋር በሰፊው ተወያይተዋል ነው የተባለው።

ባለፈው ጥቅምት 14፣ ዲሚትሪቭ ከዋሽንግተን ባለሥልጣናት ጋር ስለወደፊቱ የአሜሪካ እና ሩሲያ ግንኙነት ለመወያየት አሜሪካ መጓዛቸው ይታወሳል። ሰኞ ዕለት ከአሜሪካ ሚዲያ ጋር ባደረጉት የስልክ ቃለ-ምልልስ የአሜሪካ እና የሩሲያ ባለሥልጣናት እስረኞችን መለዋወጥ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ሲነጋገሩ ቆይተዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...