ህዳር ሲታጠን በሚል ቆሻሻ ማቃጠል እንደማይቻል ተገለፀ 

Date:



ለረጅም ዓመታት በኢትዮጵያ ህዳር 12 ቀን ሲከናወን የቆየው አከባቢን በማጽዳት ቆሻሻን የማቃጠል ስርዓት አሁን ላይ የተከለከለ ድርጊት መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ የአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን አስታውቋል።

በያዝነው ህዳር ወር በመዲናዋ በየትኛውም አከባቢ ህዳር ሲታጠን በሚል ቆሻሻን ሰብስቦ ማቃጠል በሕጉ መሰረት የሚያስቀጣ መሆኑን የገለጹት በአዲስ አበባ ከተማ የአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን የአከባቢ ብክለት ክትትል እና ቁጥጥር ዘርፍ ቡድን መሪ ወይዘሮ ሰናይት ተስፋዬ ናቸው፡፡

ይህንን ለማስፈጸም የደምብ ማስከበር ባለስልጣን ባለሙያዎችን ማዘጋጀቱን ተናግረዋል፡፡

ህዳር ሲታጠን የሚለውን ስርዓት በተሻለ መንገድ መተግበር ይገባል የሚሉት የዘርፉ ቡድን መሪዋ፣ በእለቱ የአዲስ አበባ ጽዳት አገልግሎት በሁሉም አከባቢዎች ቆሻሻ የመሰብሰብ መርሃ ግብር እንደሚያከናውን አስታውቀዋል።

ቡድን መሪዋ ማንኛውም ግለሰብ ቆሻሻ በማቃጠል አከባቢውን ብሎም መዲናዋን ከሚበክል ድርጊት መቆጠብ እንዳለበት አሳስበዋል፡፡

ከያዝነው ሳምንት ሰኞ ጀምሮ በተለያዩ አካባቢዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ እየተሰራ መቆየቱን እና እስከ ህዳር 12 ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን አስታውቋል።

[መነኻሪያ ሬዲዮ]

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...