ሩሲያ ሂውማን ራይትስ ዎችን አገደች

Date:

ሩሲያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ቢሮ ሂውማን ራይትስዎች የተባለውን የመብት ተሟጋች ድርጅት ሩሲያ “የማይፈለጉ ድርጅቶች”ብላ ከሰየመቻቸው ድርጅቶች ዝርዝር ውስጥ አካቷል።

የጀርመኑ የዜና ምንጭ ዲፒኤ እንደዘገበው፤ ርምጃውሂውማን ራይትስ ዎች በሩሲያ ውስጥ ያለውን ማንኛውንም እንቅስቃሴ ወዲያውኑ እንዲያቆም የሚያደርግ እና በሩሲያ ውስጥ ያሉ ሰዎች ወይም ድርጅቶች ከድርጅቱ ጋር መስራትንም ሕገ-ወጥ ያደርጋል።

ሂዩማን ራይትስ ዎች ከሶስት አስርት አመታት በላይ ከድህረ-ሶቪየት ሩሲያ በኋላ ያለው መንግስት ሰብዓዊ መብቶችን እና ነጻነቶችን እንዲያስከብር ግፊት አድርጓል።

ሩሲያ ዋና ዋና ነጻ የዜና አውታሮችን እና የመብት ቡድኖችን ጨምሮ ከ270 በላይ ድርጅቶችን “የማይፈለጉ” ስትል ሰይማለች።

ሂውማን ራይትስ ወች የሩስያን ጦርነት አጥብቆ ሲተች የቆየ ሲሆን፤ የጦር ወንጀለኞች ናቸው ያላቸውን ዝርዝርም መዝግቧል።

በቅርቡ የሩስያ ወታደሮች ሰላማዊ ሰዎችን በሰው አልባ አውሮፕላኖች መግደላቸውን በምርመራ ይፋ አድርጓል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...