“ ደጋፊዎች በነቂስ ወጥተው እንደሚደግፉን ተስፋ አደርጋለሁ “

Date:

የኢትዮጵያ ወጣት ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ቤንጃሚን ዚመር ዛሬ ደጋፊው በነቂስ ወጥቶ እንዲያበረታታቸው ጠይቀዋል።

የኢትዮጵያ ከ 17ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ዛሬ ከዩጋንዳ ጋር ወሳኝ ጨዋታውን ያደርጋል።

ከጨዋታው በፊት አስተያየታቸውን የሰጡት አሰልጣኝ ዚመር “ ደጋፊው በነቂስ ወጥቶ እንደሚደግፈን ተስፋ አደርጋለሁ “ ሲሉ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

ቡድኑ ጥሩ ዝግጅት ማድረጉን ያነሱት አሰልጣኙ ለዩጋንዳ ክብር እንደሚሰጡ ገልፀው እነሱ በእግርኳሱ ጥሩ እየሰሩ ያሉ ናቸው ሲሉ ተደምጠዋል።

“ ቡድኑ ተረጋግቶ እንዲፎካከር ሰርተናል “ ያሉት አሰልጣኙ “ የተቻላቸውን ጥረት በማድረግ ለሀገራቸው በፍቅር እንዲጫወቱ አሳስበናል ብለዋል።

የቡድኑ አምበል ቢኒያም አብረሀ በበኩሉ “ ከዚህ በፊት እንዳደረጋችሁት ዛሬም ድጋፋችሁን ስጡን እንጠብቃችኋለን “ ሲል ለደጋፊው መልዕክቱን አስተላልፏል።

@tikvahethsport    

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...