Date:

“የእብድ ውሻ በሽታ የህብረተሰብ ጤና ችግር እየሆነ መጥቷል” – የአማራ ክልል ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት

ባለፉት ሰባት ወራት ከእብድ ውሻ በሽታ ጋር በተገናኘ ከ30 በላይ ሰዎች ህይወታቸው እንዳለፈ የአማራ ክልል ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታውቋል።

በበሽታው የሚጠቁ ሰዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ ከፍ እያለ መምጣቱ የተገለጸ ሲሆን በየሳምንቱ ከአንድ መቶ በላይ ሰዎች በእብድ ውሻ በሽታ ተጋላጭ እንደሆኑም ተመላክቷል።

የአማራ ክልል ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የእብድ ውሻ በሽታ የህብረተሰብ ጤና ችግር እየሆነ መጥቷል ሲል ገልጿል ሲል ሀገሬ ቴሌቪዥን ዘግቧል።

ውሾችን በጊዜ አለማስከተብ እና ህብረተሰቡ ለክትባት ያለው ግንዛቤ አነስተኛ መሆን እንዲሁም በክልሉ ያለው የፀጥታ ሁኔታ ችግሩ እንዲባባስ እና የቅድመ መከላከል ስራዎች እንዳይሰሩ እንቅፋት ሆኗልም ተብሏል።

ቀዳሚ ጽሑፍ
ቀጣይ ጥሑፍ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...

ኧረ ፋታ ስጡን?!

መንግስት ግን" ምን ሁኑ ?" ሊለን ነው :: አጀንዳ...