የመታሰቢያ ጥሪ ለአርቲስት ነፃነት ወርቅነህ

Date:

በቅርቡ በሞት የተለየን ድንቅ የጥበብ ሰው አርቲስት ነፃነት ወርቅነህ ተወልዶ ባደገበትና የልጅነት ትዝታዎቹ ባሉበት በደብረ ፅጌ ቅዱሥ ዑራኤል ቤተክርስቲያን ታላቅ የመታሰቢያ እና የጸሎት መርሐ-ግብር ተሰናድቷል።

የአካባቢው ወጣቶች በጋራ ባዘጋጁት በዚህ መንፈሳዊ መድረክ ላይ፤ የሻማ ማብራት ስነ-ስርዓት የሚከናወን ሲሆን ብፁሃን አባቶች፣ መምህራነ ወንጌል፣ ዘማሪያን እንዲሁም የስራ ባልደረቦቹና ቤተሰቦቹ ይታደማሉ።

የአርቲስቱ አድናቂዎች፣ የጥበብ ቤተሰቦችና ወዳጆች ሁሉ በዚህ የክብር መርሐ-ግብር ላይ በመገኘት አብራችሁን እንድትሆኑ የዑራኤል አካባቢ ወጣቶች ጥሪያቸውን ያቀርባሉ።

መርሐ-ግብሩ የሚከናወንበት፦

  • ቀን፦ አርብ ጥር 15 ቀን 2018 ዓ.ም
  • ሰዓት፦ ከቀኑ 10:00 ጀምሮ
  • ቦታ፦ ደብረ ፅጌ ቅዱሥ ዑራኤል ቤተክርስቲያን (ዑራኤል)

ለወንድማችን ነፃነት ወርቅነህ የዘላለም እረፍትን እንመኛለን።

ነፍስ ይማር!

ለወዳጅ ዘመድዎ በማጋራት መረጃውን ያድርሱ።

Via የደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኤል አካባቢ ወጣቶች መንፈሳዊ የአገልግሎት ማህበር ነን

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...