ቻይና የሱማሊላንድን መገንጠል አልደግፍም ስትል አስታወቀች

Date:

ቻይና ሱማሊላንድ እና ታይዋን እያደረጉት ያሉትን ግንኙነት በፅኑ ተችታለች።

ከቅርብ ግዜያት ወዲህ ተገንጣይ አገራቱ ትብብራቸውን ለማጠናከር እንደሚሰሩ በተለያየ መንገድ ሲገልፁ ነበር።

ይሁንና በሱማሊያ የቻይና አምባሳደር የሆኑት ዋንግ ዩ ፤ ግንኙነታቸውን ተገንጣይነትን ለማስተዋወቅ የተጠነሰሰ ብለውታል።

‹‹በአለም ላይ ያለው አንድ ቻይና ነው፡፡ ታይዋንም የቻይና አንድ አካል ናት፡፡ በርካታ አገራት የቻይናን አንድነት ይደግፋሉ›› ያሉት አምባሳደሩ መሠረታዊው እውነትም ይሄ ነው ብለዋል።

አክለውም የሱማሊያን ሉአላዊ አንድነት ለማስጠበቅ የቤጂንግ መንግስት ከሱማሊያ ፌዴራል መንግስት ጋር በቅርበት እየሰራ እንደሚገኝ ነው የገለፁት ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመረጃ ነጻነት አዋጅን በሙሉ ድምፅ አጸደቀ

በምክር ቤቱ የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ እውነቱ...

በቬንዝዌላ በደረሰ የመሬት መንቀጥቀጥ የ32 ሰዎች ህይወት አልፏል

በቬንዙዌላ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የታወጀ ሲሆን 7.2 እና 7.5...

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ “ሉሲ” ላገኟት ፕሮፌሰር የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሰጠ

የዩኒቨርሲቲው ሴኔት ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ፥...

የሳህለወርቅ ዘውዴ አዲሱ አለም አቀፍ ሹመት በተመድ ልዩ ተልእኮ ተሰጣቸው

የቀድሞዋ የኢትዮጵያ ፕሬዝደንት ወይዘሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ በተመድ ዋና ፀሀፊ...