መንግሥት የትግራይ ተፈናቃዮችን በአፋጣኝ ወደቀያቸው መመለስ አለበት ሲል የሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም አሳሰበ

Date:

በትግራይ ክልል ተፈናቅለው የሚገኙ ዜጎችን መንግሤት በአፋጣኝ ወደቀያቸው መመለስ እንደሚገባው የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም ትግራይ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት አሳስቧል። በክልሉ ከሱዳንና ጠለምት ወረዳ ተመልሰው የመጡትን ሳይጨምር 970 ሺህ አካባቢ ተፈናቃዮች እንደሚገኙ የገለጹት የጽ/ቤቱ ኃላፊ ፀሀዬ እንባየ፤ በቂ ድጋፍም እየተደረገላቸው አለመሆኑን በሰጡት ቃል አስታውቀዋል።

የመጠለያ ድንኳንም  ከተሰራ ሦስትና አራት ዓመት አስቆጥሮ ያረጀ በመሆኑ፤ በጨርቅና ላስቲክ ሸፍነው እየተጠቀሙ እንደሚገኝም ገልጸዋል።አክለውም “የተፈናቃዮች አለመመለስ በትምህርት ስርዓቱና ሌሎች ማህበራዊ ሕይወቶች ላይ ችግር እየፈጠረ በመሆኑ መንግሥት ለጉዳዩ ትኩረት መስጠት አለበት” ብለዋል።

በመሆኑም ይህ ሁሉ ችግር ሊቀረፍ የሚችለው ግን ወደ ቀያቸው መመለስ ሲችሉ ብቻ እንደሆነ አፅንኦት ሰጥተዋል።አሐዱም “የአሜሪካ ዓለም አቀፍ ተራድኦ ድርጅት (USAID) እርዳታ ማቋረጡን ተከትሎ በተለይም ተፈናቃዮች ላይ ምን አይነት ተፅዕኖ ሊያሳድር ይችላል?” ሲል የጠየቀ ሲሆን፤ ኃላፊው በምላሻቸው ቀድሞውኑ የነበረው ችግር እየተባባሰ እንደሚሄድ ስጋታቸውን ገልጸዋል።

በእርዳታ ሰጪዎች አማካኝነት ለጥቂቶች ብቻ ድጋፍ ሲደረግ ለብዙሃኑ እንደተደረገ ተደርጎ መረጃ ስለሚሰራጭ ይሄ በራሱ ተፈናቃዮች ላይ ጫና ሲፈጥር የቆየ መሆኑን በማንሳት፤ በውጪ እርዳታ ተመርኩዞ የሚደረግ ድጋፍ ዘላቂ ስለማይሆን ዋነኛው መፍትሄ መንግስት በራሱ አቅም ማገዝ ሲችል እንደሆነም ኃላፊው ጨምረው ተናግረዋል።

@Ahadu

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...