የንግድ ውድድር እና የሸማቾች ጥበቃ አዋጅ መሻሻያ ሊደረግለት ነው

Date:

በሸማቾች ላይ የሚፈፀምን የመብት ጥሰት ምላሽ ይሰጣል የተባለ የንግድ ውድድር እና የሸማቾች ጥበቃ አዋጅ መሻሻያ ሊደረግለት መሆኑ ተገልጿል።

ይህን ያሉት በንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር የሸማች መብት ጥበቃና የግንዛቤ ፈጠራ ዴክስ ሃላፊ አቶ ሰይፉ አየለ ከጣቢያችን ጋር በነበራቸው ቆይታ ነው።

አቶ ሰይፉ የንግድ ውድድር እና የሸማቾች ጥበቃ አዋጅ የሸማቾችን መብት ከመጠበቅ አንፃር መደረግ የሌለባቸውንና ያለባቸውን ተግባራት በመዘርዘር አስቀምጧል ነው ያሉት።

ይሁንእና ማሻሻያ ያልተደረገለት አዋጁ የመብት ጥሰት በሸማቹ ላይ ሲደርስ፣አላስፈላጊ የዋጋ ጭማሪ ሲኖር ፣ በምርቶች ላይ አግባብነት የሌለው ባእድ ነገር ሲያጋጥም ሸማቹ መብቱን ለማስከበር የሚያልፍበት ሂደት አሰልቺ እንደሆነ አንስተዋል።

ይህን ችግር ለመፍታት አዋጁን በማሻሻል በአፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።

በዚኛው ማሻሻያ ሸማቹ ወዲያውኑ ብዙ ሳይደክም ምላሽ የሚያገኝበትን አሰራር መዘርጋቱን አንስተዋል።

የንግዱን ህብረተሰብ ከፀረ-ውድድር እና ተገቢ ካልሆኑ የገበያ ተግባራት እንዲሁም ሸማቹን ከሚያሳስቱ የገበያ ሁኔታዎች የሚከላከልና ለነፃ ገበያ ውድድር አመችነት ያለው ሥርዓት መዘርጋት አስፈላጊ መሆኑ ተነስቷል ፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመረጃ ነጻነት አዋጅን በሙሉ ድምፅ አጸደቀ

በምክር ቤቱ የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ እውነቱ...

በቬንዝዌላ በደረሰ የመሬት መንቀጥቀጥ የ32 ሰዎች ህይወት አልፏል

በቬንዙዌላ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የታወጀ ሲሆን 7.2 እና 7.5...

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ “ሉሲ” ላገኟት ፕሮፌሰር የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሰጠ

የዩኒቨርሲቲው ሴኔት ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ፥...

የሳህለወርቅ ዘውዴ አዲሱ አለም አቀፍ ሹመት በተመድ ልዩ ተልእኮ ተሰጣቸው

የቀድሞዋ የኢትዮጵያ ፕሬዝደንት ወይዘሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ በተመድ ዋና ፀሀፊ...