“ያለ አፍሪካ አውሮፓ ብሩህ የወደፊት ተስፋ ሊኖራት አይችልም”! የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ

Date:

የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ አፍሪካ የዓለም የታሪክ መድረክ ዋና ተዋናይ እየሆነች መምጣቷን በመግለጽ፣ ያለ አፍሪካ ንቁ ተሳትፎ ጣሊያንም ሆነች አውሮፓ ብሩህ የወደፊት ተስፋ ሊኖራቸው እንደማይችል ገለጹ።

በንግግራቸው አህጉሪቱ ያላትን ሰፊ የተፈጥሮ ሀብት፣ የእርሻ መሬት እና ወሳኝ የሰው ኃይል በአግባቡ መጠቀም እንደሚገባ ያሳሰቡት ጠቅላይ ሚኒስትሯ፤ ጣሊያን በአውሮፓ እና በአፍሪካ መካከል እንደ ድልድይ ሆና ለማገልገል ዝግጁ መሆኗን አረጋግጠዋል።

በተለይም ወጣቶች በቴክኖሎጂ እና በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ዘርፍ እንዲሰለጥኑ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።

ይህም የአፍሪካን ተሰጥኦ ወደ ውጭ ከመውሰድ ይልቅ በአህጉሪቱ ውስጥ እንዲያድግ የሚያደርግ አዲስ የልማት ሞዴል እንደሆነ ገልጸዋል።

የአፍሪካ ዜጎች በገዛ ሀገራቸው የመኖር እና የመሥራት ነፃነት ሊኖራቸው እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል።

ወጣቶች በስደት ሀገራቸውን ሲለቁ የሚፈጠረውን የታሪክ እና የባህል ክፍተት ለመሙላት ጥራት ያለው ትምህርት፣ የሥራ ዕድል ፈጠራ እና ጠንካራ የኢንዱስትሪ ትብብር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል።

ስደትን እንደ ብቸኛ አማራጭ ማየት “ራስ ወዳድነት” መሆኑን የጠቀሱት ሜሎኒ፤ የማይቻለውን ነገር በትብብር ወደ እውነት ለመለወጥ እና ዓለምን ለማስደመም ቃል ገብተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ሜሎኒ ንግግራቸውን ሲያጠቃልሉ “ሁልጊዜም ከአፍሪካ አዲስ ነገር ይገኛል” የሚለውን ጥንታዊ አባባል በመጥቀስ ለአዲሱ የአጋርነት መንፈስ ያላቸውን ቁርጠኝነት ገልጸዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

“ሕገ መንግሥታዊ ተቃርኖዎች”:-  ከዳኛ ፍሬሕይወት ሳሙኤል ጋራ ውይይት

ዳኛ ፍሬሕይወት ሳሙኤል በተለይ በ1997 ዓ.ም በተደረገው ምርጫ 97...

የ12ኛ ክፍል የፈተና ቀን ታወቀ

የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሠርተፊኬት (12ኛ ክፍል ፈተና) ከሰኔ...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከሳልቫ ኬር ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አደረጉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከደቡብ ሱዳን ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት...

አሜሪካ ኤርትራ ላይ የጣለችውን ማዕቀብ ልታነሳ ነው !

የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር፣ አሜሪካ ከኤርትራ ጋር ያላትን ግንኙነት...