89ኛው የየካቲት 12 ሰማዕታት መታሰቢያ በዓል ተከበረ

Date:

የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማህበር 89ኛውን የየካቲት 12 ሰማዕታት መታሰቢያ በዓል በስድስት ኪሎ በሚገኘው የሰማዕታት መታሰቢያ ሐውልት ፊት ለፊት አክብሯል። በበዓሉ ላይ አባትና እናት አርበኞች በመገኘት የአበባ ጉንጉን በማኖር የሰማዕታቱን መስዋዕትነት ዘክረዋል።

የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማህበር ፕሬዝዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን፤ ወጣቱ ትውልድ አያትና ቅድመ አያቶቹ ለሀገር ፍቅርና ለአንድነት የከፈሉትን የሕይወት መስዋዕትነት በማሰብ፣ ሀገሩን ከጠላት ጥቃት እንዲጠብቅና ልማቷን እንዲያስቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።

ኢትዮጵያ በየጊዜው በውስጥ ባንዳዎችና በውጭ ጠላቶች ሰላሟን ለማደፍረስና ሕዝቧን አንገት ለማስደፋት የሚደረጉ ሙከራዎችን በልጆቿ ጀግንነት ስታከሽፍ የኖረች፣ በደሟ ታፍራና ተከብራ የቆየች ሀገር መሆኗንም ፕሬዝዳንቱ አክለው ገልጸዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የባህልና ኪነ-ጥበብ ቢሮ ምክትል ኃላፊ ዶ/ር አዲሱ ሻንቆ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ በትውልድ ቅብብሎሽ በነፃነቷ ጸንታ የኖረች ሀገር መሆኗን ጠቅሰው፣ ዛሬ ደግሞ በልማት አዲስ ታሪክ ለመጻፍ በምታደርገው ጥረት ሁሉም በተሰማራበት ዘርፍ ርብርብ ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢራን ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን በድጋሚ መዝጋቱን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ

የኢራን መገናኛ ብዙኃን የአገሪቱ ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን ዳግም መቆጣጠር...

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት ክብረ በዓል

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አስመልክቶ...

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለ20 አትሌቶች  የማስጠንቀቂያ አውጥቷል

በውድድሩ ላይ ያልተገኛችሁ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይመለከታል የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዓለምአቀፍ...

የአሜሪካ እና የኢራን ድርድር፤ ለወረራ የታለመ ማደናገሪያ? ሩሲያ ማስጠንቀቂያ ሰጠች!

በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው ዲፕሎማሲያዊ ንግግር ውጥረትን ለመቀነስ...