ኢራን በሆርሙዝ ሰርጥ ላይ የሚንቀሳቀሱ መርከቦችን ለመምታት ዛተች

Date:

ቴህራን እስራኤል እና አሜሪካ የከፈቱትን ጥቃት ተከትሎ በዓለም ወሳኙ የነዳጅ ዘይት መተላለፊያ በሆነው የሆሙዝ የባሕር ሰርጥን ላይ ለማለፍ በሚሞክሩ መርከቦች ላይ ጥቃት እንደምትፈጽም ዛተች።

አንድ ኢራን ባለሥልጣን በሆሙዝ ሰርጥ “ለማለፍ የሚሞክር ማንኛውም መርከብን በእሳት ነው የምንለኩሰው” ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

ማስጠንቀቂያውን የሰጡት ባለሥልጣን የኢራን እስላማዊ አብዮት ዘብ ዋና አዛዥ አማካሪ የሆኑት ኢብራሂም ጃባሪ በአገሪቱ ብሔራዊ ቴሌቪዥን ቀርበው በተናገሩበት ወቅት ነው።

የሆርሙዝ ሰርጥ መዘጋቱን ያስጠነቀቁት ባለሥልጣኑ መርከቦች “ወደ ቀጠናው መምጣት የለባቸውም። ከባድ የሆነ ምላሽ ከእኛ ይጠብቃቸዋል” ሲሉ ዝተዋል።

ጃባሪ አሜሪካ “የቀጠናውን የነዳጅ ዘይት ተጠምተዋል” ያሉ ሲሆን ኢራን “በቀጠናው የሚገኙ የነዳጅ ማስተላለፊያ ቧንቧዎችን ታጠቃለች፤ ከቀጠናው ነዳጅ እንዲላክ አትፈቅድም” ብለዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በአንድ ዓመት ውስጥ ቃል የተገቡ 417 የዓይን ብሌኖች ለሆስፒታሎች ተሰራጩ

​ የኢትዮጵያ የደምና ሕብረ ህዋስ ባንክ አገልግሎት በተጠናቀቀው የ2018 በጀት...

በኢትዮጵያ በውርስና ስጦታ ላይ አዲስ ታክስ ሊጣል ነው

በኢትዮጵያ በውርስና ስጦታ ላይ አዲስ ታክስ ሊጣል ነው በኢትዮጵያ...

ትምህርት ሚኒስቴር ለአዲሱ ዓመት 11 አዳዲስ የሙያ ትምህርት ዓይነቶችን ይፋ አደረገ

​የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና ከክልል...

የአዲስ አበባ ጉዳይ በሌሎች አጀንዳዎች ላይ የሚካሄደውን ምክክር ጥላ አጥሎበታል

ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በ25ኛ ቀን ውሎው በሥራ ቡድን ደረጃ...