በአማራ ክልል 308 የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ሊገነቡ ነዉ

Date:

የክልሉ ትምህርት ቢሮ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር 308 ደረጃቸውን የጠበቁ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ሊገነባ መሆኑን የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ገልጿል ።

የቢሮዉ ኃላፊ አቶ ጥላሁን ወርቅነህ ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት 154ቱ ትምህርት ቤቶች በፌደራል ትምህርት ሚኒስቴር በጀት ድጋፍ የሚገነቡ ሲሆን የተቀሩት 154 ደግሞ በወረዳና ህብረተሰቡ ተሳትፎ የሚገነቡ ናቸዉ ።

እነዚህም 308 ትምህርት ቤቶች በሚቀጥሉት ስድስት ወራት ሁሉም ግንባታቸዉ ተጠናቆ ለ2019 የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር አገልግሎት እንደሚሰጡ አቶ ጥላሁን ጨምረዉ ለጣቢያችን ተናግረዋል።

አሁን ላይ የተቋራጭ ልየታ ስራ እየተከናወነ መሆኑን የገለፁት ኃላፊዉ  የትምህርት ጥራት ችግርን በዘላቂነት ለመፍታትና ብቁና ተወዳዳሪ ዜጎችን ለመፍጠር ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ማስፋፋትና ማጠናከር ላይ በትኩረት እየተሰራ ነዉ ብለዋል ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር የሚያደርጉት ድርድር እስኪጠናቀቅ ድረስ የተኩስ አቁሙ መራዘሙን አስታወቁ

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በፓኪስታን ጥያቄ መሠረት ከኢራን ጋር የገቡትንየተኩስ...

ለኢትዮጵያ የግብርና ዘርፍ የሚውል የ40 ሚሊዮን ዩሮ የገንዘብ ድጋፍ ተፈቀደ

የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ የልማት ክንፍ የሆነው ኢአይቢ ግሎባል (EIB...

ሃይንከን በአልኮል መጠኑ ጠንከር ያለ ቢራ ለኢትዮጵያ ገበያ አስተዋወቀ

ሃይንከን ኢትዮጵያ በእለም አቀፍ ደረጃ ዝነኛ የሆነውን ዴሰፔራዶስ (Desperados)...