የረመዳን ወር ድሆችን፣ ችግረኞችንና ስደተኞችን በመደገፍ ማሳለፍ ይገባል

Date:

የረመዳን ወርን ከድሆች፣ ችግረኞች እና ስደተኞች ጋር በጋራ በመብላት፣ በመጠጣትና በመደገፍ ማሳለፍ ይገባል ሲሉሉ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሼኽ ሐጅ ኢብራሂም ቱፋ አስገነዘቡ።

6ኛው ሀገራዊ የጎዳና ላይ ኢፍጣር መርሐ ግብር በአዲስ አበባ ከተማ መስቀል አደባባይ ተካሂዷል።

ሼኽ ሐጅ ኢብራሂም ቱፋ በመርሐ ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት አንድነትን በተግባር የሚያሳየው የጎዳና ላይ ኢፍጣር መርሐ ግብር አስደሳች መሆኑን ገልጸው÷ የረመዳን ወር የቸርነት ወር በመሆኑ ከድሆች፣ ችግረኞችና ስደተኞች ጋር በጋራ ማሳለፍ ይገባል ብለዋል።

የእምነቱ ተከታዮች ለሀገራችን፣ ለወገናችን፣ ለአፍሪካ እና ለዓለም ሰላም ዱዓ ማድረግ ይገባል ብዋል።

በመርሐ ግብሩ ከፍተኛ የመንግሥት ስራ ኃላፊዎች፣ አምባሳደሮች፣ ዲፕሎማቶችና የሐይማኖቱ ተከታዮች ተገኝተዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...

ኧረ ፋታ ስጡን?!

መንግስት ግን" ምን ሁኑ ?" ሊለን ነው :: አጀንዳ...