በኬንያ የጣለው ከባድ ዝናብ የ42 ሰዎችን ህይወት ቀጠፈ

Date:

በኬንያ ለቀናት የዘለቀው ከባድ ዝናብ ባስከተለው የጎርፍ አደጋ የ42 ሰዎች ህይወት ማለፉን መንግስት አስታውቋል።

ካለፈው ዓርብ ጀምሮ የጣለው ዝናብ በተለይ በዋና ከተማዋ ናይሮቢ የ26 ሰዎችን ህይወት የቀጠፈ ሲሆን፣ በመላ ሀገሪቱም በመሰረተ ልማት እና በዜጎች ኑሮ ላይ ከፍተኛ ውድመት አድርሷል።

የሀገሪቱ የልዩ ፕሮግራሞች ሚኒስትር ጄፍሪ ሩኩ እንደገለጹት፣ ጎርፉ መንገዶችን በማጥለቅለቅ የትራንስፖርት እና የእለት ተእለት እንቅስቃሴን ሙሉ በሙሉ አስተጓጉሏል።

በናይሮቢ መደበኛ ባልሆኑ ሰፈሮች የሚገኙ መኖሪያ ቤቶች እና ተሽከርካሪዎች በጎርፍ የተወሰዱ ሲሆን፣ የአየር በረራዎችም ወደ ሞምባሳ እንዲቀየሩ ተገደዋል።

ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ለተጎጂ ቤተሰቦች መጽናናትን ተመኝተው፣ ወታደራዊ ሃይልን ጨምሮ የተቀናጀ የነፍስ አድን ስራ እንዲከናወን ትዕዛዝ አስተላልፈዋል።

አሁንም ዝናቡ ሊቀጥል ስለሚችል ነዋሪዎች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ የደህንነት አካላት እያሳሰቡ ይገኛሉ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...