በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች የሚታየውን የኤሌክትሪክ መቆራረጥ በ27 በመቶ የሚቀንስ የ4.3 ቢሊዮን ብር ግዙፍ የኃይል ማሻሻያ ፕሮጀክት እየተከናወነ ይገኛል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እንዳስታወቀው፣ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብድር የሚተገበረው ይህ የአዴሌ (ADELE) ፕሮጀክት በአሁኑ ወቅት 36.74 በመቶ አፈፃፀም ላይ ደርሷል።
ሥራው 703 ኪሎ ሜትር የኔትዎርክ መስመር ዝርጋታን፣ የ2 ሺህ አዳዲስ ትራንስፎርመሮችን ተከላ እና የሌሎች 2 ሺህ ነባር ትራንስፎርመሮችን አቅም የማሳደግ ተግባራትን ያካትታል።
በኮንክሪት ምሰሶና በሽፍን ኬብል የሚከናወነው ይህ ግንባታ የትራንስፎርመር መቃጠል አደጋን በእጅጉ የሚቀንስ ሲሆን፣ አስተማማኝና ቀጣይነት ያለው የኃይል አቅርቦት ለነዋሪዎች ለማድረስ ያለመ እንደሆነ ተገልጿል።
